Search This Blog

Thursday, November 24, 2016

በእነ ጉርሜሳ አያኖ የክስ መዝገብ 3ኛ ተከሳሽ በሆነው አዲሱ ቡላላ ላይ የዓ/ህግ ምስክር ተሰማ

የኦፌኮ ም/ፕሬዚደንት አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ በእነ ጉርሜሳ አያኖ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ የቀረበባቸው 22 ሰዎች ላይ የፌደራል አቃቤ ህግ ያቀረባቸው ምስክሮች ቀርበው እየተሰሙ ሲሆን፤ ህዳር 14/2009 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ አንድ የዐቃቤ ህግ የደረጃ ምስክር በ3ኛ ተከሳሽ አቶ አዲሱ ቡላላ ላይ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
መዝገቡን እያየ ያለው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት ጠዋት ላይ ተሰይሞ የነበረ ቢሆንም የ2ኛ ተከሳሽ ጠበቃዎች በወቅቱ ባለመኖራቸው የምስክር ማሰማቱ ሂደት ለከሰአት ተዘዋውሯል።
የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት አስተዳደር እያደረሰባቸው ያለውን ሰብአዊ መብት ጥሰት በተመለከተ ተከሳሾች በጠበቃቸው አማካኝነት አቤቱታቸውን በፅሁፍ ለፍርድ ቤቱ አስገብተው እንደነበረ የሚታወስ ነው፤ የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር በበኩሉ አቤቱታው ከእውነት የራቀ እንደሆነ፤ እንዲያውም የተከሳሾች ጠበቃ የማረሚያ ቤቱን ስም የማጥፋት ስራ እየሰሩ መሆኑን በመጥቀስ ምላሽ በፅሁፍ አስገብተዋል።
በጠዋቱ ችሎት ተከሳሾቹ ያቀረቡት አቤቱታ የሚመለከታቸው የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሃላፊ የሆኑት ሱፐር ኢንቴንደንት ጣእመ በችሎት ውስጥ በመገኘታቸው ዳኞቹ በአካል ቀርበው እንዲያስረዱ ተደርገው፤ ሃላፊው አቤቱታ አቅራቢዎቹ የሚሉት ነገር ከእውነት የራቀ እንደሆነ እና ስለ ጉዳዩ እንደማያውቁ ተናግረው ከሌሎች የስራ ባልደረቦቻቸው ጋር በመነጋገር ችግር ካለ እንደሚፈቱ ተናግረዋል።
FREE ALL POLITICAL PRISONERS !!!
በተለይም 6ኛ፣ 7ኛ፣ 14ኛ እና 17ኛ ተከሳሾች (ገላና ነገራ፣ ጭምሳ አብዲሳ፣ ደረጄ መርጋ እና ገመቹ ሻንቆ) ለቂሊንጦ ማረሚያ ቤት መቃጠል እጃችሁ አለበት ተብለው ቀንና ለሊት እጃቸውን እና እግራቸውን በካቴና ታስረው እንደሚያድሩ፣ ከቤተሰብ እንደማይገናኙ፣ከውሃ እና ሳሙና አንፃር ከቤተሰብ እንዳይቀበሉ መደረጋቸው በፅሁፍ ካቀረቡት አቤቱታ በተጨማሪ በችሎት ውስጥም በምሬት ተናግረዋል።
አራቱ ተከሳሾች ጉዳዩ ይመለከተኛል ብለው ለችሎት ምላሽ የሰጡትን ሃላፊውን ጭራሽ አይተዋቸው እንደማያቁ እና የተናገሩትም ትክክል እንዳልሆነ ተናግረዋል። 14ኛ ተከሳሽ የሆነው አቶ ደረጄ መርጋ ካቴናው እጁ ላይ ከመክረሙ የተነሳ አልከፈት ብሏቸው ከእጁ ካቴናው ሳይወልቅ ችሎት እንዳስገቡት እጁን ከነካቴናው ከፍ አድርጎ ለችሎት አሳይቷል። በሰአቱ ዳኞች በአስቸኳይ እንዲፈታለት ለማረሚያ ቤት ፓሊሶች ቢያዙም፤ ፓሊሶቹ ካልተቆረጠ በቀር መክፈት እንደማይቻል አስረድተው ከነካቴናው ችሎቱን ጨርሷል። እንዲሁም 7ኛ ተከሳሽ ጭምሳ አብዲሳ ካቴናው እጁን ከማጥበቁ የተነሳ እጁ መቁሰሉን ለችሎት አሳይቷል። በካቴና ለ24 ሰአት ከመታሰር በተጫማሪ ያሉበት ክፍል 24 ሰአት ተዘግቶ አንደሚቀመጡ፣ በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ 84 እረኞች ተጨናንቀው እየኖሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል። 14ኛ ተከሳሽ አቶ ደረጄ “በቃጠሎ አላችሁበት ተብለን ሸዋሮቢት ተወስደን ስለ ደረሰብንን ድብደባ እና እንግልት እየተናገርን አይደለም፤ እሱን ታሪክ የሚጠይቃችሁ ይሆናል። በአሁኑ ሰአት ማረሚያ ቤቱ አስተዳደር የሚያደርስብን በደል ግን እንዲቀርልን፤ እንደ ሰው እንድንቆጠር ነው የምንጠይቀው።” በማለት ጥያቄውን አሰምቷል። ዳኞች ደረሰብን የሚሉትን የመብት ጥሰት ለማረሚያ ቤቱ የበላይ አካል የአመልክተው ያውቁያ እንደሆነ አራቱን ተከሳሾቹን ጠይቀው፤ ተከሳሾቹ 24 ሰአት የክፍላቸው በር ተዘግቶ እና በካቴና ታስረው ስለሚቀመጡ ለበላይ አካል ማመልከት የሚባለው ነገር የሚታሰብ አለመሆኑን አስረድተዋል። ዳኞቹ ረዘም ያለ ጊዜ ወስደው ሃላፊውን ሱፐር ኢንቴንዳንት ጣእመን፤ ተመሳሳይ አቤቱታዎችም በሌሎች መዝገቦች እየቀረቡ መሆናቸውን ጠቅሰው የተጠርጣሪዎቹን መብት መጣስ ማንንም እንደማይጠቅም እና እንዲህ አይነቱ ተግባር የሃገሪቱ የፍትህ ስርአት ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እንደሚያመጣ ዘርዘር አድርገው አስረድተዋቸዋል፤ ተጠርጣሪዎቹ የተከሰሱበት ወንጀል በፍርድ ቤት የተያዘ ጉዳይ ስለሆነ ሌላ ቅጣት እና የመብት ጥሰት ተገቢም እንዳይደለ መክረዋል። በመጨረሻም ዳኞቹ ተከሳሾቹ በምስክር የመስማት ሂደት ተከሳሾቹን በየሚቀጣይ ቀናትም በተከታታይ የሚያገኟቸው በመሆኑ በቀረበው አቤቱታ ላይ የሚታዩ ለውጦች ካሉ እናያለን በማለት ሃላፊውን በነገው እለትም እንዲቀርቡ በማዘዝ የጠዋቱን ችሎት ዘግተዋል።
በከሰአቱ ችሎት አቃቢ ህግ ዳኞች ከተሰየሙ በኋላ ዘግይቶ በመድረሱ ዳኞች ሌላ ጊዜ እንዳያረፍድ አስጠንቅቀውታል። አቃቤ ህግ በበኩሉም ምስክሮችን ጥበቃ እንደቆየ አስረድቷል። አቃቤ ህግ በእነ ጉርሜሳ አያኖ መዝገብ 3ኛ ተከሳሽ በሆነው አቶ አዲሱ ቡላላ ላይ ሁለት የደረጃ ምስክሮች እንደቀረቡ አስረድቷል። ምስክሮቹ አቶ ታደሰ ታፈሰ እና አቶ አሸናፊ ደጀኔ እንደሚባሉ እንዲሁም ምስክሮቹ የሚመሰክሩበትን ጭብጥም አሲዟል። ጭብጡ— ጥር 17/2008 ዓም ቀን ከጠዋቱ 3:30 ላይ አዲሱ ቡላላ በፌደራል ወንጀል መመርመሪያ ማእከል ከፌስቡክ አካውንቱ ፕሪንት የተደረጉ መረጃዎችን የተከሳሽ ስለመሆናቸው የታዘቡትን በወቅቱ የታዘቡትን እንዲመሰክሩ ነው። አቃቤ ህግ የመጀመሪያውን ምስክር አቶ ታደሰ ታፈሰ የምስክር ቃላቸውን እንዲሰጡ ካስጠሯቸው በኋላ ምስክሩ ቃለ መሃላ ፈፅመው የአቃቤ ህግን ዋና ጥያቄ በመመለስ ቃላቸውን መስጠት ጀምረዋል። ምስክሩ ተነስተው ተከሳሹን አዲሱ ቡላላን በአካል እንዲያሳዩ በአቃቤ ህግበ ተጠይቀው 22ቱ ተከሳሾች የተቀመጡበት ቦታ ሄደው ሁሉንም ካዩ በኋላ አዲሱ ቡላላ ነው በማለት 8ኛ ተከሳሽ የሆነውን አቶ ጌቱ ግርማን አሳይተዋል። መሳሳታቸው በዳኞች ከተነገራቸው በኋላ ምስክሩ የተሳሳቱት ተከሳሹን ካዩት ረዘም ያለ ጊዜ ስለሆነ ነው ብለው ለማስረዳት ሞክረዋል። ጥር 17/2008 ዓም ከጠዋቱ 3:30 አካባቢ የፌደራል ወንጀል መመርመሪያ ማእከል ለስራ ከሌላ ባልደረባቸው ጋር (ባልደረባቸው በአዲሱ ቡላላ ላይ ሌላኛው ምስክር ናቸው) በሄዱበት ወቅት ቢሮ ቁጥር 31 ውስጥ አዲሱ ቡላላ ቢሮ ውስጥ የነበረውን ገመዶቹ ተነቃቅሎ የነበረ ኮምፒውተር እንደሰካካ እና እንዳበራ እንዲሁም የፌስ ቡክ አካውንቱን ስም እና የይለፍ ቃል በፈቃደኝነት አስገብቶ ከጃዋር መሃመድ ጋር መልእክት የተለዋወጠባቸውን ፅሁፎች 54 ገፅ ፕሪንት መደረጉን፤ ፕሪንት ከተደረጉ በኋላም አዲሱ ከፈረመባቸው በኃላ እሱ እና ሌላኛው ምስክር (የስራ ባልደረባቸው) መፈረማቸውን ተናግሯል። ስለ ፅሁፉ ይዘት ተጠይቀው በአብዛኛው በላቲን የተፃፈ በመሆኑ እንዳልተረዱት ነገር ግን በእንጊሊዘኛ ከተለዋወጧቸው መልእክቶች አዲሱ 38 የሚሆኑ እስረኞች በማረሚያ ቤት እንዳሉ ለጃዋር ሲነግረው ጃዋርም ለእስረኞቹ የሚሆን ብር እንደሚልክ የሚገልፁትን መልእክቶች እንደሚያስታውሱ ተናግረዋል። ፈረምኩባቸው ያሏቸውን ሰነዶችም ከሌሎች የማስረጃ ሰነዶች ውስጥ ለይተው አሳይተዋል። ምስክሩ ቃላቸውን በሚሰጡበት ወቅት “ያለበት ሁኔታ ነው ያለው” እና “እንትን” የሚሉ ቃላቶችን በተደጋጋሚ በሚጠቀሙበት ወቅት ዳኞች ምንም እንኳን የተለመዱ አባባሎች ቢሆኑም ገላጭ ባለመሆናቸው እንዳይጠቀሟቸው ቢያሳስቧቸውም፤ ምስክሩ በተለይም “ያለበት ሁኔታ ነው ያለው” የሚለውን ሃረግ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተው እስኪጨርሱ ድረስ ይጠቀሙት ነበር። ምስክሩ በአቃቤ ህግ ስራቸው ምን እንደሆነ ሲጠየቁ የመንግስት ስራ እንደሚሰሩ ብቻ በመናገር ቢያልፉም የተከሳሹ ጠበቃ አቶ አመሃ የት እንደሚሰሩ እና የስራ ድርሻቸውን በጠየቋቸው ወቅት ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር ውስጥ የስራ አስኪያጁ አማካሪ በመሆን እንደሚሰሩ ተናግረዋል። በተመሳሳይ መልኩ ከአቃቤ ህግ ለምን ጉዳይ ማእከላዊ እንደተገኙ ሲጠየቁ ለስራ ጉዳይ ብለው በደፈናው ከመለሱ በኋላ በጠበቃ አመሃ ለምን የስራ ጉዳይ እንደሆነ እንዲያብራሩ ሲጠየቁ ከፀጥታ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ችግር ፈጣሪዎች ስለነበሩ የነሱን ጉዳይ ለመጠቆም እንደሆነ ተናግረዋል።
የአዲሱ ቡላላ የፌስ ቡክ በስሙ እንዳይደለ፣ ፌስቡክህን ክፈት ተብሎ መርማሪ ሲጠይቀው ዴካ አንበሳ የሚል ስም ያለው አካውንት እንደከፈተ እና ከጃዋር መሃመድ ጋር የተለዋወጡት መልእክትም በዚሁ አካውንት እንደሆነ ነገር ግን አዲሱ ራሱ የራሴ የምጠቀምበት አካውንት ነው ሲል እንደሰማው አስረድተዋል። ጠበቃ አመሃ ዴካ አንበሳ የሚለውን ስም እንዴት ሊያስታውስ እንደቻለ ሲጠይቁት በማስታወሻ ደብተር ይዞት እንደነበረ እና ለምስክርነት ሲጠራ ማስታወሻውን አይቶ እንደመጣ ያስረዳ ሲሆን ጃዋር መሃመድን ግን በዝና ስለሚያውቀው ስሙን ለማስታወስ እንዳልተቸገረ ተናግሯል። በዝና ስትል ምን ማለትህ ነው ተብሎ ከዳኞች ለቀረበለት የማጣሪያ ጥያቄ ፤ ጃዋር ከሽብር ጋር በተያያዘ በሚዲያዎች በተደጋጋሚ ስለሚቀርብ ነው የሚል ምላሽ ሰጥቷል። በወቅቱ የጃዋር መሃመድ ፕሮፋይል ፒክቸር ከማስተር ፕላኑ ጋር ተያይዞ ሴይ ኖ የሚል የተቃውሞ የመፈክር የሚነበብበት ምስል እንደሆን፤ የአዲሱ ቡላላ ዴካ አንበሳ የሚለው አካውንት ደግሞ የሴት ምስል እንደነበረው እንደሚያስታውሱ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ምስክሩ ተከሳሽን ከተጠቀሰው ቀን በፊትም በኋላም እንደማያቋቸው፣ ቢሮ ቁጥር 31 እሳቸው እና የስራ ባልደረባቸው ሲገቡ ተከሳሹ አዲሱ ቡላላ እና መርማሪው ብቻ እንደነበሩ፣ ቢሮ ውስጥ ከሁለት በላይ ኮምፒውተሮች፣ ጠረጴዛዎች እና አንድ ፕሪንተር እንደነበረ እንደሚያስታውስ ተናግሯል።

Friday, November 18, 2016

ETHIOPIA COURT SENTENCES UNIVERSITY STUDENTS TO VARIOUS TERMS IN JAIL

The Federal High court 19th criminal bench has yesterday sentenced three of the five university students, who were arrested in April-May 2014 during the first #OromoProtests, to various terms in jail.
Six university students from various universities located in Oromia regional state were among the hundreds of students arrested during the April-May 2014 Oromo students protests against the now shelved Addis Abeba Integrated Master Plan. They were subsequently charged with violating various articles in Ethiopia’s sweeping Anti-Terrorism Proclamation (ATP). One of the six, Lenjissa Alemayehu, a third-year water engineering student at Jimma University, was acquitted by the court during the early days of the trial, although he has been in and out of prison since. The remaining five were charged for having connections with the outlawed Oromo Liberation Front (OLF), and for inciting violence during the students’ protests.
In December 2015, the federal high court 19th criminal bench found all the five guilty of the charges against them. Accordingly, the first defendant, Abebe Urgessa, was found guilty of being behind the May 2014 football stadium explosion that went off at Haromaya University, in eastern Ethiopia, killing one and injuring over 40. However, during the last two trials last week and this week, prison police have failed to bring Abebe from Showa Robit prison, some 200k northeast of Addis Abeba. The court adjourned the sentencing of Abebe until November 28th next week.
The 2nd, 3rd and 4th defendants, students Megersa Worku, Adugna Kesso and Billisuma Damana respectively, were found guilty of violating article 7/1 of the ATP, whereas the 5th defendant student Teshale Bekele was found guilty of violating article 257/A of the criminal code.
During yesterday’s hearing, the court sentenced the 3rd and 4th defendants Adugna Kesso and Billisuma Damana to four years and five months each.

Wednesday, November 16, 2016

BEKELE GERBA ET AL –FEDERAL COURT OVERRULES PROSECUTOR’S REQUEST FOR CLOSED WITNESS HEARING

In a rare and unexpected decision, the federal high court 18th criminal bench has today overruled prosecutors’ request for closed hearing of witnesses in the case involving senior opposition party members Bekele Gerba and Dejene Fita Geleta, first secretary general and secretary general of the opposition Oromo Federalist Congress (OFC). Accordingly, the court has decided to preside over all the judicial matters related to the case, under the file name of Gurmesa Ayano, in open court.  
On Tuesday, Nov. 15, prosecutors have submitted a letter to the court detailing their concerns for the safety of witnesses. In the letter, prosecutors have said that because of the seriousness of the case, their witnesses were under pressure.  The letter also stated that some of the witnesses were people who have participated in the alleged crimes are they were scared of appearing in person to testify. It also said some of the witnesses live in same areas where the defendants are from and therefore fear for the safety of their relatives.
letter-of-request-for-closed-hearing
The court overruled all the three points in the letter and has begun hearing witnesses’ testimonials as of this morning. Accordingly, four witnesses have testified against the 2nd and 3rd defendants, Dejene Tafa and Addisu Bullala, as well as the 8th and 12th defendants Getu Girma Tesfaye Liben, respectivelyAll the four witnesses were people who have been present during searches by police officers of defendants’ computers, emails, and Facebook accounts as well as houses and could only confirm their presences during the searches.
The court adjourned the next witnesses’ hearing against the remaining 18 defendants for the coming two consecutive days.

Sunday, November 13, 2016

“እሰነጥቅሃለሁ ተብያለሁ ” አቶ በቀለ ገርባ | የአቃቤ ህግ ምስክሮች አልተሰሙም፤ የቂሊንጦ ማ/ቤት ተጠርጣሪዎችን አሟልቶ አላቀረበም

Free Bekele Gerba!!!
የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ህዳር 2/2009 ዓ.ም በዋለው ችሎት ላይ እንደተመለከተው በእነ ጉርሜሳ አያኖ የክስ መዝገብ ከተካተቱት ተጠርጣሪዎች (22 ሰዎች) መካከል 5ቱን ማ/ቤቱ አላቀረባቸውም፡፡ የቂሊንጦ ማ/ቤት አስተዳደር ህዳር 2/2009 ዓ.ም ለፍርድ ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ እንደገለጸው ‹4ቱ ተጠርጣሪዎች በቂሊንጦ የደረሰውን የእሳት ቃጠሎ አደጋ ተከትሎ ሸዋሮቢት ማ/ቤት ተወስደው ስላልተመለሱ› ማቅረብ አልቻለም፡፡ ማ/ቤቱ ሸዋሮቢት እንደሚገኙ ያመለከታቸው ተጠርጣሪዎች ገላና ነጋሪ፣ ገመቹ ሻንቆ፣ ደረጀ መርጋ እና ቶምሳ አብዲሳ ናቸው፡፡
ሆኖም ግን ማ/ቤቱ በስም ጠቅሶ ሸዋሮቢት ስለሆኑ ማቅረብ አለመቻሉን ከጠቀሰው ሌላ አንድ ተጠርጣሪ ችሎት አለመገኘቱን በማጣራት ፍ/ቤቱ ተጠርጣሪውን ለምን እንዳላቀረበ የማ/ቤቱን ተወካይ ጠይቋል፡፡ ሆኖም የዕለቱ ጉዳይ አስፈጻሚ ም/ሰርጀንት ዘውዱ ወልደማርያም ተጠርጣሪው በእርግጥ የት እንደሚገኝ እንደማያውቁ ተናግረዋል፡፡ ይህ የት እንዳለ ያልታወቀው ተጠርጣሪ ጭምሳ አብዲሳ ይባላል፡፡
በዛሬው የችሎት ውሎ ተጠርጣሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ጠበቆችም ተሟልተው አለመቅረባቸው ታውቋል፡፡ የብዙዎቹ ተጠርጣሪዎች ጠበቃ የሆኑት አቶ ወንድሙ ኢብሳ አልቀረቡም፡፡ ተከሳሾችም ጠበቃቸው ከቀጠሮ በፊት ደንበኞቻቸውን ለማነጋገር ወደቂሊንጦ ሄደው ማግኘት እንደማይችሉ ተነገሯቸው መመለሳቸውን ከማወቃቸው ውጭ በዛሬው ችሎት ለምን እንዳልቀረቡ እንደማያውቁ ለችሎቱ ተናግረዋል፡፡ በችሎት የቀረቡት ሌሎች ጠበቆችም ቢሆን ቂሊንጦ ማ/ቤት ደንበኞቻቸውን በነጻነት ስለጉዳያቸው ለማነጋገር እንዳይችሉ እንቅፋት እየፈጠረባቸው መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ችሎቱ ዛሬ የተሰየመው የአቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት መሆኑን በመጥቀስ አቃቤ ህግ ከአጠቃላይ 42 ምስክሮቹ መካከል አምስቱ መቅረባቸውን በመግለጽ ምስክሮቹ ቀርበው እንዲሰሙለት ጠይቋል፡፡ ሆኖም ግን ተከሳሾቹ ሁሉም ተሟልተው ባልተገኙበት ሁኔታ ምስክር ሊሰማ እንደማይገባ ጠቅሰው ተቃውመዋል፡፡ ተከሳሾቹ በክሱ ላይ በጋራ የቀረበባቸው ፍሬ ነገር ስላለ በተናጠል ምስክሮች ቢደመጡ መብታችንን ይነካል በሚል በጠበቆቻቸው አማካኝነት አስረድተዋል፡፡
በሌላ በኩል አቶ በቀለ ገርባ አሁን ጉዳያቸውን እየየ የሚገኘው ችሎት በክስ መቃወሚያቸው ላይ ጉዳያቸው በፌደራል ፍ/ቤት ሳይሆን በኦሮሚያ ክልል ፍ/ቤቶች ሊታይ ይገባል በሚል ያነሱትን ህገ-መንግስታዊ የመብት ጥያቄ በጣሰ መልኩ ሐምሌ 25/2008 ዓ.ም መቃወሚያቸውን ውድቅ ማድረጉን በማስታወስ፣ በፍ/ቤቱ ገለልተኝነት ላይ ጥያቄ ስላላቸው ችሎት ቀርበው ክርክር ለማድረግ እንደማይፈልጉ ቀደም ብለውም ገልተጸው እንደነበር ጠቅሰው በዛሬው ችሎት ላይም ፖሊስ በጉልበት እየደበደበ እንዳቀረባቸው አስረድተዋል፡፡
አቶ በቀለ ሌሎችንም ተከሳሾች በመወከል እንዳስረዱት ከዚህም በኋላ ችሎት የሚቀርቡ ከሆነ ተገደው እየቀረቡ እንዳሉ ችሎቱ እንዲያውቅላቸው ጠይቀዋል፡፡ ፍ/ቤቱ ውድቅ ያደረገባቸውንና በክስ መቃወሚያ የጠቀሱትን ይህንኑ የህገ-መንግስት ጉዳይ ከጠበቆቻቸው ጋር ተመካክረው ወደ ፌደሬሽን ም/ቤት የመውሰድ ሀሳብ እንዳላቸውም ጠቅሰዋል፡፡
Politician Mr Bekele Gerba in court
ፖሊስ በጉልበት መኪና ውስጥ ካስገባን በኋላ ‹‹እሰነጥቅሃለሁ›› የሚል ዛቻ እንደደረሰባቸው፣ ይህን የተናገረውን ፖሊስ ችሎት ፊት ጠቁመው በማሳየት ጭምር ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ግን ይህን ዛቻ ያደረሰውን ፖሊስ ችሎቱ አንድም ጥያቄ ሳያቀርብለት አልፎታል፡፡
በመጨረሻም ፍ/ቤቱ በዛሬው ውሎ ያልቀረቡ ተከሳሾችን ማ/ቤት እንዲያቀርብ፣ 7ኛ ተከሳሽ ጭምሳ አብዲሳን ማ/ቤት ለምን እንዳላቀረባቸው ምክንያት እንዲያስረዳ እንዲሁም የኦሮምኛና ስዋህሊ ቋንቋዎች አስተርጓሚዎች እንዲመደቡ ትዕዛዝ በመስጠት ተከሳሾቹ ተሟልተው ሲቀርቡ የአቃቤ ህግ ምስክሮችን ለመስማት ለህዳር 6/2009 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ፍ/ቤት ማንኛውም ተከሳሽ በቀጠሮው ዕለት የፍ/ቤቱን ትዕዛዝ አክብሮ መገኘት እንዳለበትም ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡
በዛሬው የችሎት ውሎ የኦሮምኛ ቋንቋ አስተርጓሚ ችሎቱ ባለማቅረቡ ከተከሳሾች መካከል አቶ በቀለ ገርባ በአጋዥነት ሲያስተረጉሙ ውለዋል፡፡

Wednesday, November 9, 2016

Crossing Arms: The Plight and Protest of the Oromo

 #OromoRevolution Crossing Arms: The Plight and Protest of the Oromo
We need freedom!!!
Accurate information on African politics and culture is extremely difficult to attain. Western countries routinely delegitimize African professionals and news outlets by sharing biased accounts of issues occurring in African countries to African people. I have done my absolute best to adequately research and interview inorder to offer the most accurate account of the political situation in Ethiopia and plight of the Oromo people.
Following a year of protests carried out by the Oromo people, the Ethiopian government announced a state of emergency in effect for at least six months. The reason cited as violence and unrest among the country’s largest ethnic group. However, the party conducting the offensive is in question. Members of the Oromo community claim that government forces are using excessive brutality to stamp down revolts following what they claim are violations of human and civil rights as well as unjust seizure of private land.
The Oromo community makes up nearly fourty million people, mainly residing within the borders of Ethiopia. The Horn of Africa, a pastoral hub, is continuously marred by its colonial history; one of the main factors creating ethnic, economic, political, and social instability today. Their colonization and fusion into Ethiopian society disrupted the established and independent, political structure of the Oromos while also placing a massive ethnic group in a subordinate position to two other smaller ethnic groups, the Amhara and Tigray.
The current political group in power, The Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), is facing scrutiny for its treatment of minority groups. Following the establishment of the 1994 Constitution, after Eretria’s secession and independence, local and international sources began to suspect that the members of the Tigray People’s Liberation Front (TPLF), later reorganizing into the EPRDF, manipulated the country’s constitution for its own aims:
“The TPLF-dominated EPRDF intentionally included Article 39 [The right to secession] in Ethiopia’s 1994 Constitution so that the Tigray region could loot Ethiopia of its resources, use the Ethiopian military to expand the borders of Tigray, and then secede from Ethiopia”.
Under the false impression that the TPLF/EPRDF are adequately democratic entities, the global community continues to uphold support and offer aid to the government. In the 2015 general elections, the ERPDF won one hundred percent of parliamentary seats. in the previous election the party won 99.6%. Election results like this one reveal that the government is, in all reality, authoritarian, masking their lack of democratic principles with elections as well as the elimination of rivaling civil society groups and independent media. Peaceful, anti-government protests erupted across the Amhara and Oromia regions following the election results. Between November 2015 and August 2016, at least 500 protesters were killed by security forces and thousands detained under terrorism charges.
Successive government leaders have been cited by Human Rights Watch and Non-Governmental Organizations (NGOs) for human rights abuses as well as non-democratic and severe “iron-fistedness” against dissension; such as, “the Charities and Societies Proclamation of 2008. This restricts Ethiopian non-governmental organizations from embarking on any human rights-related work if they receive their funding from foreign source” according to Adeyinka Makinde of Global Research. The EPRDF has the capacity to stamp down any and all forms of dissension due to its “full control of the security apparatus, the military, the police force and the intelligence services, dominated by ethnic Tigrayans”. EPRDF also legitimizes the use of extreme force under its “vaguely drafted counter-terrorism laws”.
Why Now?
The most recent protests and government crackdown have entered international focus with figures such as Olympic silver-medalist Feyisa Lilesa crossing his arms in solidarity with the Oromo people during the Rio 2016 Olympics.
The Oromo people endured oppression for the past century; the question remains as to why, finally, the Oromo peoples’ protests have gained traction.
In an interview with Gemechu Mekonnen, an undergraduate student studying at the University of Minnesota Twin Cities, an Ethiopian, and an Oromo, he explained that the oppression of the Oromo people reached a tipping point around a year ago when the government planned to enact what is coined “The Master Plan” to seize Oromia land. Farmers around the capital would in turn, lose their source of income with little to no compensation while the government sold their property, arguably for some the most fertile land in Africa, to foreign investors such as China.
The lack of representation, subjugation and oppression of the Oromo group by ethnic groups such as the Ahmara and Tigray resulted in an “unsurprising amount of frustration and resentment”. the Ethiopian government had, “already taken the dignity, voice, and lives of so many, [that] the Oromo people finally said ‘enough is enough’ to the government’s unjust actions”.
Understanding a country’s history and human rights record, while necessary, is not sufficient to comprehend the opinions, needs, and future of an ethnic group. Mekonnen’s insight offers a rare and intimate perspective on the plight of the Oromo people, their tenacity, and their unwavering battle for self-determination:
“The ‘why now’ really comes rooted in many different now. Whether it’s the influence of globalization revealing more of the world to Ethiopians [and to] Oromos, the emboldened and educated students and youth [who] question the status quo, or the blatant lack of respect for the land and life of their people, all these [factors] were important in catalyzing the active voices for change that now exist. The more the government tries to arrest journalist, suppress independent media, and kill opposition leaders, the more the people protest”.
The more pressure the international and domestic community puts on the government, the greater the voice the Oromo people have to advocate or their rights domestically and on a global stage. However, signs of progress are small and incremental. On October 2nd 2016, an estimated 678 civilians were killed and countless injured by government forces in what is now infamously known as The Irreecha Massacre. Nearly two million people from across Oromia assembled to celebrate Irreecha, a festival marking the changing of seasons. Irreecha, for many Oromo, is a setting for “resistance and reaffirmation of identity” where attendees sing revolutionary songs and denounce human rights abuses. Following what the attendees considered a politicization of the festival, an individual openly defied the organizers (who were affiliated with the government) and spoke out against the EPRDF. Security forces responded by firing bullets and tear gas on the unarmed participants. Repeatedly hearing news about the tragic loss of life of his people leaves Mekonnen feeling “a sense of hopelessness”. He describes “a recurring feeling dread, not for what could happen to me, but for what is most likely happening to the family I have in Ethiopia”.
The situation in Ethiopia reaches far beyond its borders. The Oromo peoples’ struggle, while inadequately understood by the rest of the world, is catalyzing what will be true, grass-roots changes. There remains much reform that needs to be done regarding Oromo self-determination