Search This Blog

Thursday, November 6, 2014

ህዳር 9: የጸረ-ጭቆና ኣመጽ ዕለትን በተመለከተ ከኦነግ የተሰጠ መግለጫ

ለኦሮሞ ህዝብ የነጻነት ትግል የበለጠ ህዝባዊ ድጋፍ ለማስገኘትና ለጭቆና ስርዓት ፍጻሜ ለማበጀት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር በ2005ዓም “በጨቋኝ የባዕዳን ስርዓት መገዛት ይብቃን!” ብሎ በጠላት ላይ እንዲያምጽ ለመላው የኦሮሞ ህዝብ ጥሪ ኣስተላለፈ። የኦሮሞ ህዝብም ከነጻነት ታጋይ መሪ ድርጅቱ፡ ኦነግ፡ የተላለፈለትን ጥሪ በደስታ ተቀብሎ በመላው ኦሮሚያ ውስጥ የጸረ-ጭቆና ኣመጽ በማካሄድ ዘወትር ሲዘከር የሚኖር ኣኩሪ እርምጃ ወሰደ።
በ2005ዓም የተቀጣጠለው ኣመጽ በተለያየ መልክና ደረጃ ሲካሄድ ዛሬ መድረሱም በተጨባጭና በገሃድ እየታየ ነው። በቀጣይነት እየተካሄደ ያለውን ይኸው የ2005ቱ የጸረ-ጭቆና ኣመጽም ከወርሃ ሚያዚያ 2011ዓም ጀምሮ በቆራጥ የቄሮ ኣባላት የኦሮሞ ወጣቶች በኣዲስና የተደራጀ መልክ ይዞ ይበልጥ በመፋፋም መላውን ኦሮሚያን ኣዳርሶ እንደቀጠለ ነው። በቄሮ ቢሊሱማ የኦሮሞ ወጣቶች ተቀጣትሎ በሰፊው የኦሮሞ ህዝብ ተሳትፎና ድጋፍ እየተካሄደ ያለው ኣመጽ ጠላትን ያንቀጠቀጠና የኦሮሞ ህዝብ የነጻነት ትግልን ደግሞ ወደ ግቡ ያቃረበ መሆኑ በ2014ዓም ሲካሄድ የነበረውና እየተካሄደያለው የጸረ-ጭቆና ኣመጽ በሚገባ ኣረጋግጧል።
በኦሮሞ ወጣቶች ግንባር-ቀደም ተሳትፎ እየተካሄደ ያለው የኦሮሞ ህዝብ ኣመጽ በሃገር-ቤትና በውጪ ሃገራት ካለው የኦሮሞ ተወላጅ ከፍተኛ ድጋፍና ትብብር ማግኘት መቻሉ በኦሮሞ ህዝብ ላይና በኦሮሚያ ወስጥ እየተፈጸመ ያለውን ደባና እኩይ ተግባራትን ለዓለም ይፋ ማድረግ ኣስችሏል። እነዚህ ድሎች በቀላሉ ያልተገኙ ስለመሆናቸው ደግሞ ከማንም የተሰወረ ኣይደለም። የኦሮሞ ህዝብ ነጻነትን የሚፈልግ መሆኑን በግልጽ ለማሳየት ከባድና ውድ መስዋዕትነት ከፍሏል። ህይወቱ፡ ኣካሉንና ንብረቱን እንዲሁም በገንዘብ የማይተመኑ ሌሎች መስዋዕትነቶችን እየከፈለ ይገኛል። ከሁሉም በላይ በኢትዮጵያ ኢምፓዬር ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የቄሮ ቢሊሱማ ኣባላት የኦሮሞ ወጣቶች ለሃገር ባለቤትነት መብታቸው መከበር ሲያካሄዱት የነበረውና እያካሄዱት ያለው ፍልሚያ ጨቋኙን የወያኔ ስርዓት እየለበለበ፡ የኦሮሞ ህዝብ ነጻነት የማይቀር መሆኑን በግል ኣስመስክሯል። የኦሮሞ ህዝብ ነጻነት መረጋጋጥ የማይቀር መሆኑን መተኪያ የሌላትን ህይወታቸውን በመሰዋት ያረጋገጡትን የኦሮሞ ወጣቶች፡ ተማሪዎችና ብሄርተኞችን በክብር መዘከር ደግሞ የሁሉም የኦሮሞ ዜጋ የዜግነት ግዴታ ነው።
የዘንድሮውን ህዳር 9: የጸረ-ጭቆና ኣመጽ ዕለት በኦሮሚያ ውስጥና የኦሮሞ ዜጎች በሚገኙባቸው የውጪ ሃገራት ሁሉ በደመቀ ሁኔታ ህይወታቸውን የሰዉትን ውድና ቆርጥ የኦሮሞ ልጆች ከማሞገስና መዘከር በተጨማሪ መስዋዕትነት የከፈሉበትን የነጻነት ትግል ከግቡ ለማድረስ ቃላችንን ማደስ ይኖርብናል። በዚህም ለፍትሓዊና ክቡር ዓላማ ልጆቻቸውን ያጡትን እናቶች እንባ ለማበስ ይበልጥ ለመታገል በቆራጥነት መነሳት ይጠበቅብናል። ለህዝባቸው ነጻነት ሲሉ በጸረ-ጭቆና ኣመጹ ውስጥ ህይወታቸውን የሰዉትን የኦሮሞ ወጣቶች፡ ተማሪዎች ብሄርተኞችን መዘከር የያንዳንዱ ኦሮሞ ዜጋ ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ ይህንን ዕለት በያለንበት ሁሉ እንዘክር። የተሰዉ ጀግኖቻችንን ስናስታውስ የጨቋኙ ስርዓት ወህኒ ቤቶች ውስጥ እየተሰቃዩ ያሉትን ዜጎቻችንንም መርሳት የለብንም። በተቻለ መንገድ ሁሉ ከጎናቸው መቆም ሁሉም የኦሮሞ ዜጋ በተጨማሪ ሊተገብረው የሚገባ ወገናዊ ግዴታ ነው። ጨቋኙ የወያኔ መንግስት ለኦሮሞ ህዝብ ርህራሄ የሌለውና ኦሮሞን ከምድረ-ገጽ በማጥፋት እንደጨቆነ ለመኖር ኣቅዶ እየሰራ ያለ መሆኑ ያለፉት 23ዓመታት የወይኔ ኣገዛዝ በማያጠራጥር ሁኔታ ኣሳይተዋል።
ስርዓቱ የኦሮሞ ህዝብን ለማጥፋት ከመስራት የማይቆጠብ መሆኑን የኦሮሞ ዜጎችን ያለምንም ርህራሄ ከኣያት-ቅድመ ኣያት መሬታቸው በማፈናቀል ለራሱ መውሰድና ለሸሪኮቹ ማከፋፈል፡ ኦሮሞ በኢኮኖሚ ጠንካራ መሰረት እንዳይኖረው የተለያዩ ደባዎችን በመፈጸም ማደህየት፡ የኦሮሞ ልጆችን ከማሃይምነት ጨለማ ውስጥ ለማስቀረት ከየትምህርት ቤትች በጅምላ ማባረር፡ በእስርቤቶች ውስጥ ማሰቃየትና እየፈጸመ ያለው ጭካኔ የተመላበት ግድያ ለዚህ ማርረጃ ይሆናሉ።
በሌላ በኩል የኦሮሞ ህዝብን በተለያየ በልኩ ሊቀርቡትና ሊወዳጁት የሚሹ ባዕዳን ሁሉ ነጻነቱና የዲሞክራሲ መብቱ ተከብሮ እንደኦሮሞ በሃገሩ ላይ ኣዛዥ ሆኖ መኖሩን የማይፈልጉ መሆናቸውን የጸረ-ጭቆና ኣመጹ በሚገባ ኣረጋግጧል። የኦሮሞ ዜጎች የነገ ሃገር ተረካቤ የወገን ኣለኝታ ወጣቶች ሳይቀሩ በጠራራ ጸሃይ በጥይት ሲደበደቡ፡ በኣስር ሺዎች እስር ቤት ሲታጎሩ፡ ህጋዊ ኣግባብ የረዥም ዓመታ የእስር ብይን ሲተላለፍባቸ ለኦሮሞ ዜጎች ኣለመረሳቸውና በዝምታ ማለፋቸው እነዚን ባዕዳን ኣካላት ምን እንደሚፈልጉ ያሳያል።
ትላንት፡ ዛሬም ሆነ ለወደፊቱ የኦሮሞ ህዝብ የነጻነት ትግል በባዕዳን ኣካላት ትብብርና ድጋፍ ሳይሆን በራስ በመመኮዝ ዓላማ በመካሄድ ፍጻሜውን የሚያገኝ መሆኑ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር የጸና እምነት ነው። ስለሆነም የኦሮሞ ህዝብ በተለይም ደግሞ የታጠቀውን የጠላይ ሃይል ባዶ እጆቹን በጀግንነት እየተጋፈጠ ያለው ኣዲሱ ትውልድ ነጻነቱን የሚያገናጽፈው ትግሉ ብቻ መሆኑን በጥልቀት በመገንዘብ ኣመጹን ኣፋፍሞ ከፍጻሜው ኣንዲያደርስ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር በዚህ ኣጋጣሚ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
በሃገር ቤትና ውጪ ሃገራት ያለው የኦሮሞ ህዝብም እንደኣሁኑ ኣንድነቱን ኣጠናክሮ የጋራ ክንዱንም በማጠናከር የጸረ-ጭቆና ኣመጹን በማፋፋሙ ውስጥ ድርሻውን እንዲያሳድግ ኦነግ በክብር ያሳስባል። ጠንካራ ሃይል ሆነን የጭቆናን ቀንበር ኣሽቀንጥረን ለመጣል እንድነታችንን እናጠናክር።
የወይኔ መንግስት በኣሁኑ ወቅት ኣገዛዙን ለማስቀጠል ስልጣን ላይ የሚያሰነብተውን የይስሙላ ምርጫ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ለሰኔ ወር ቀጠሮ የተያዘለት ምርጫ ካሁን ቀደም ከተካሄዱት ምርጫዎች የተለየ ይሆናል የሚል እምነት የለውም። የምርጫውን መድረክ የሚያዘጋጀው፡ የሚመራውና የሚመረጠውን ሰው የሚያዘጋጀው ወያኔና ወያኔ ብቻ ነው። ከዚህ ደግሞ የኦሮሞ ህዝብ ኣንዳች ፋይዳ ኣግኝቶ ኣያውቅም፡ የሚያገኘው ጥቅምም ኣይኖርም። ስለሆነም የኦሮሞ ህዝብ ዘወትር በሚነዛው የጠላት ፕሮፓጋንዳ ሳይታለል በማይመለከተው ምርጫ ላይ ጊዜውን ማባከኑን ትቶ የኣልገዛም-ባይነት ኣመጹን ኣጠናክሮ እንዲቀጥል ኦነግ መልዕክቱን ያስተላልፋል። ለጠላት ሰርግ ኣጫፋሪ መሆን እዚህ ላይ ማብቃት ይኖርበታል።

Angola journalist criticizes African Union

The African Union should move its headquarters out of Ethiopia because of concerns about freedom of expression there, an Angolan journalist and human rights campaigner said.
Journalist Rafael Marques de Morais, who has been jailed and faces numerous legal challenges for his investigative work in Angola, said in Johannesburg on Tuesday night that the African Union is hypocritical for keeping its base in Addis Ababa, the Ethiopian capital. The union represents 53 countries on the continent and says it is committed to transparency and human rights.
Marques cited the ongoing Ethiopian trial on terrorism-related charges of bloggers from Zone 9, a collective that publishes critical news and commentary. He also mentioned the three-year prison sentence handed last week to Temesgen Desalegn, the former editor of the now-defunct newspaper Feteh who was convicted of charges including incitement.
"The situation has worsened, and it indeed shows the hypocrisy of the African Union as an organization representing all Africans," Marques said at an African journalism conference held at the University of the Witwatersrand.
The Committee to Protect Journalists says there are at least 17 journalists in jail in Ethiopia. The only African country with more journalists in prison is Eritrea, it said.
African journalists and human rights campaigners should be "embarrassed for doing so little to support our peers in Ethiopia," Marques said. One option, he said, is to campaign to get the African Union to move its headquarters to a country with a good human rights record.
The Angolan journalist gave a lecture held annually in honor of Carlos Cardoso, a Mozambican journalist who was fatally shot in 2000 in Maputo, Mozambique's capital, while investigating

በምርጫ ሥም የነጻነት ትግሉን ማዘናጋት አይቻልም!!

የ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› ህዝባዊ ትግል ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር እንቅስቃሴ በፓርቲዎች ትብብር በህዳር ወር ይጀመራል!
ከኢትዮጵያ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ትብብር የተሰጠ መግለጫ
ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም ትብብር የመሰረትን ዘጠኝ ፓርቲዎች ስለምስረታችን በሰጠነው መግለጫ የስምምነታችን ‹‹ … ዘላቂ ግብ ማንም ተጎጂ የማይሆንበትና ሁላችንም ተጠቃሚ የምንሆንበትን አቅጣጫ የተከተለ እንደመሆኑ ገዢው ፓርቲ/መንግስት እኔ ከሥልጣን ከለቀቅሁ በቀጣይ በሚመጣው ለውጥ አገር ትበታተናለች በማለት ህዝብን ከሚያስፈራራበት፣ ካድሬዎቹን ፣መከላከያ ሠራዊቱንና የፀጥታና ደህንነት ኃይሉን ተቃዋሚዎች ካሸነፉ አንድም ለወህኒ ካነሰም ‹‹ለልመናና የጎዳና ተዳዳሪነት›› ትዳረጋላችሁ… በሚል ሽብር ከሚነዛበት ፕሮፖጋንዳና አካሄድ እንዲመለስና እንዲታረም ዕድል የሚሠጥ›› መሆኑን ፣ ለትብበሩ አባላት ‹‹ ከምንም እና ከማንም በላይ ቀዳሚው አገርና ህዝብ ›› መሆኑንና በህዝባዊ ሠላማዊ ትግል በምትገነባው ሉዓላዊነቷ የተከበረ ዲሞክራሲዊት ኢትዮጵያ ‹‹ በሁለት ጽንፎች የተወጠረው የአገራችን የአሸናፊ-ተሸናፊ የጠቅላይ ሥልጣን ፖለቲካ ልምድ እንደሚቀየርና በከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ በህዝቦች መካከል ያለውን አብሮነት ለመበጣጠስ የተዘራውን አጥፊ ዘር ማድረቅ፣ የተሰራጨውን መርዝ ማርከስ ›› መቻሉን መግለጻችን ይታወሳል፡፡
አካሄዳችንን በሚመለከትም ‹‹…ለጋራ ዓላማችን እውን መሆን ያለፈው አካሄዳችን የትም እንዳላደረሰንና እንደማያደርሰን ከውድቀታችን ልምድ ቀስመን በአዲስ አስተሳሰብና የአመራርና አሰራር ሥርዓት ለማይቀረው ሥር ነቀል ሁለንተናዊ ለውጥ በግልጽነት በተጠያቂነት መርህ በጽናት ለመታገልና ለማታገል የደረስንበትን ስምምነት ስናበስር ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚመጣውን አገራዊና ህዝባዊ ኃላፊነት በመገንዘብ ›› መሆኑን ገልጸን ለዓላማችን ማስፈጸሚያ ተመጋጋቢና ተደጋጋፊ የአጭርና የረጅም ጊዜ የዕቅድ አቅጣጫ ማስቀመጠችንንም ገልጸን ነበር፡፡ የዛሬው መግለጫችን ዓላማም ባስቀመጥነው የአጭር ጊዜ ዕቅድ - ምርጫ 2007 ላይ ትኩረት ያደረገና ‹‹ ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል ፕሮግራም በተከታታይ የሚካሄደውን ህዝባዊ ሠላማዊ ትግል የመጀመሪያውን ዙር የአንድ ወር እንቅስቃሴ መርሀ-ግብር ከባለቤቱ ዘንድ ማድረስ ነው፡፡
በዚህ መግለጫ በአገራችን ነባራዊና ተጨባጭ ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊና ማኅበራዊ እውነታዎች ዝርዝር ውስጥ ለመግባት አይሞከርም ፣ በየቤታችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚታየውን ፣በአራቱም የአገሪቷ አቅጣጫዎች በህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ሥቃይና የሰላምና ፀጥታ ፣የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት… ላይ የደረሰውንና የፈጠረውን ሥጋት ማንሳት ‹‹ ቀባሪን የማርዳት›› ሙከራ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ትኩረታችን በምርጫና በመጪው ምርጫ 2007 ላይ ይሆናል፡፡
ሁላችንም እንደምናውቀው በመጪው ግንቦት ወር አምስተኛው አገራዊና ክልላዊ ምርጫ ይካሄዳል ተብሎ ስለሚጠበቅ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀውን የጊዜ ሰሌዳ እንደተለመደው ለማወያየት በሚል ለማሳወቅ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ስብሰባ መጥራቱ ይታወሳል፡፡ ከዚህ ስብሰባ አስቀድሞ የዚህ ትብብር አባላትን ጨምሮ አስራ ሁለት ፓርቲዎች ለቦርዱ ጥቅምት 5 ቀን 2005
‹‹ 1ኛ/ ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ያቀረብናቸው ጥያቄዎቻችን እንዲመለሱ፤
2ኛ/ ገዢውን ፓርቲና አጋሮቹን ጨምሮ ሁሉም ህጋዊ ፓርቲዎች በጋራ ተገናኝተው በምርጫና የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ግንባታ ላይ የሚወያዩበት የጋራ መድረክ እንዲዘጋጅ ››
የሚሉ የጋራ ጥያቄዎችን በማቅረብ ‹‹የእነዚህ ጥያቄዎች መልስ ማግኘት ማለት ለሠላማዊ የሥልጣን ሽግግር / የነጻ፣ ፍትሃዊና ተኣማኒና አሳታፊ የምርጫ ውድድር ሥርዓት/ ሠላማዊ ትግል/ ዕድል ከመስጠትና የመድብለ ፓርቲ ሥርዓት ከማረጋገጥ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው፡፡ ማለትም በሌሎች አምባገነን መንግስታትና ሥርዓቶች በጦር መሣሪያ ኃይልና በደህንነት አቅም በመመካት በሥልጣን ላይ ለመቆየት ያሳዩትን እምቢተኝነትና ማንአለብኝነት ተከትሎ የተከሰቱ ህዝባዊ እምቢተኝነትና በውጤታቸውም የተከተሉ ቀውሶችን በጋራ በመከላከል ከአሸናፊ/ተሸናፊ ጠቅላይ የፖለቲካ ሥልጣን አስተሳሰብ በመውጣት ለዲሞክርሲያዊ ሥርዓት ግንባታ መሠረት የመጣልና ለዘላቂ ሠላምና ልማት ዋስትና መስጠት ማለት ነው፡፡ በዚህ ማንም ተጎጂ አይሆንም፡፡›› ብለን ሌላው አማራጭ ደግሞ ‹‹በተቃራኒው እነዚህ

Tuesday, November 4, 2014

በወያኔ ባለስልጣናት እና በቅርብ ሰዎቻቸው ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤ እየታየ ነው።

የመከላከያ እና ፖሊስ ሰራዊቱ ላይ አለመተማመኑ እየጨመረ መጥቷል።
- የደህንነት አባላቱ መረጃን በግል ጥቅም በመለወጥ እየሰሩ ነው የሚል ግምገማ ቀርቦባቸው ተንጠዋል።
- የሃገሪቱን ጉዳይ በተመለከተ ለበታች "ተከታይ " ባለስልጣናት መረጃ መስጠት ቆሟል።
- የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ አይደሉም ።
በኢትዮጵያ ውስጥ መጭው ጊዜ በህዝቡ ዝምታ ተከትሎ በስርአቱ ላይ ከፍተኛ ቀውስ ይከተላል የሚል መረጃ መሰማት ከጀመረ ጀምሮ በወያኔ ባለስልጣናት እና በቅርብ ሰዎቻቸው ዘንድ ከፍተኛ የሆነ ድንጋጤ መኖሩን ምንጮች ለምንሊክ ሳልሳዊ ገልጸዋል።የአስመራ ተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ ሪሞት ኮንትሮል ወያኔ እጅ ነው ስለዚህ የትጥቅ ትግል ወያኔን አያስፈራውም ያሉት ምንጮች የሃገር ውስጥ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ወያኔ ልሙጥ የሚላቸው የተቃዋሚ ፓርቲዎቹ አጋር ዲያስፖራዎች በለውጥ እንቅስቃሴ ውስጥ ህዝቡን በማንቃት ረገድ እያደረጉት ያለው ርብርብ ትልቅ ስጋት እንደፈጠረባቸው እንዳስደነገጣቸው ሲታወቅ በድንጋጤ የመጣ ለኢሕአዴግ አንዳንድ ወቅታዊ ጥያቄዎችን እያቀረቡ ያሉ ባለስልጣናት ከሃገር እንዳይወጡ እና ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ፓስፖርታቸውን ከመነጠቅ ጀምሮ በአይነቁራኛ እንደሚጠበቁ ታውቋል። የሕወሓት ታጣቂዎች ከምቾት ኑሮ ተነስተው ለመሸሽ እንጂ ታጥቀው ደም ለመፋሰስ ዝግጁ እንዳልሆኑ ከምንጮቹ ተሰምቷል።
በመከላከያ ሰራዊቱ ውስጥ አዳዲስ የሆኑ ውስጣዊ እርምጃዎችን በመውሰድ በተጠናከረ መልኩ በሰራዊቱ መካከል እየተከሰተ ያለውን አለመተማመን ለመቆጣተር የሚረዱ ስብሰባዎች በስፋት ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ መካሄድ የጀመሩ ሲሆን በፖሊስ ሰራዊቱም ውስጥ በተለይ በቡድን የሚያሴሩ ሰዎች አሉ እየተባለ ስለሚነገር የወያኔ አንድ ብሄር ሰዎችን በስፋት በመመደብ እንዲሁም ከዚህ ቀደም እንደተሰረገው የቢሮ ሰራተኛውን ከደህንነት ቢሮ በሚመደቡ የሕወሓት ደህንነቶች ለመተካት የታቀደ ሲሆን ቀሪውን ከቢሮ ውጭ የሚሰራውን የፖሊስ አካል ለመቆጣጠር አዲስ ሃይል እንደሚመደብ ታውቋል።የመከላከያ እና የፖሊስ ሰራዊቱ ከሃገሪቱ የተቃዋሚ ሃይሎች ጋር በማበር አደጋ ሊፈጥር ይችላል ሲል መፈራቱ እንዲሁም ሰራዊቱን እየከዱ የሚሄዱ መበራከታቸው አለመተማመኑን ከማስፋቱም በላይ ጥያቄዎች እንዲነሱ አድርጓል።
በኢትዮጵያ ውስጥ እየተደረገ ያለውን የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መንግስት አቀፍ እንቅስቃሴ በተመለከተ ከሕወሓት ባለስልጣናት ውጪ ለበታች ተከታይ ባለስልጣናት ምንም አይነት መረጃ መስጠት እንደቆመ ሲታወቅ ማንኛውም ሃገራዊ ጉዳይ አልቆ እና በአፈጻጸም ደረጃ ላይ ሆኖ እንደማንኛውም ሰራተኛ እንደሚሰሙ ባለስልጣኖቹ በመናገር ላይ መሆናቸው ታውቋል ። በደህንነት ቢሮ ውስጥ በተደረገ ግምገማ የደህንነት አባላት መረጃዎችን በግል ጥቅም በመለወጥ አሳልፋቹ እየሸጣችሁ ናቸው በሚል መገምገማቸውን የውስጥ ምንጮች ተናግረዋል።እንደ ምንጮቹ ከሆነ መረጃን ያለምንም ርሕራሔ መረጃው በአምስት ደኢቃ ውስጥ ጠላት እጅ ገብቶ ያገኘነው ነው ሲሉ የአዲስ አበባው ደህንነት ሹም አቶ ጸጋዬ ተናግረዋል።በዚህ ግምገማ የተከፉት የደህንነት አባላት በመንግስት ባለስልጣናቱ እየተናጡ ቢወረፉም ዝምታን መርጠዋል።

Monday, November 3, 2014

‹‹ጥቁሩ አብዮት›› እና ኢትዮጵያ

ጌታቸው ሺፈራው
ከሳምንታት በፊት ከጓደኞቼ ጋር እስክንድር ነጋን ልንጠይቀው ወደ ቃሊቲ አቅንተን ነበር፡፡ በወቅቱ ስለ ለውጥ አውርቶ የማይጠግበውን እስክንድርን ስለ ኢትዮጵያ መጻኢ እድል ስንጠይቀው የመለሰልን ቀላል ግን ደግሞ የሚገርም መልስ ነበር፡፡ እስክንድር ተስፋ አስቆራጭ የሚመስለው ትግል ፍሬያማ ሊሆን እንደሚችልና በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚነሳው ጥያቄን ልክ እንዲህ ነበር ያስረዳን፡፡
‹‹እነ ጋናን፣ ዛምቢያን፣ እና ሌሎቹንም የአፍሪካ አገራት ነጻ እንዲወጡ ኢትዮጵያ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጋለች፡፡ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት አሁን ነጻ ካወጣቻቸው ኢትዮጵያ የተሻለ ዴሞክራሲ ገንብተዋል፡፡ እኛ እየጠየቅን ያለነው እንደነዚህ አገራት አይነት ስርዓት እንዲሰፍን ነው፡፡ የቅንጦት ጥያቄ አልጠየቅንም፡፡ መጠየቅ ከነበረብን እጅግ ትንሹን ነው እየጠየቅን ያለነው፡፡››
ከሶስት ቀናት በፊት እስክንድር እኛ ነጻ አውጥተናቸው ከእኛ ይሻላሉ ካላቸው አገራት መካከል ቡርኪናፋሶዎች ለስርዓቱ ሌላ ጥያቄ አንስተው ራሳቸው ሲመልሱት ስመለከት ያስታወስኩት እስክንድርን ነው፡፡ እኛ ምንም ጥያቄዎች ሳይመለስልን እነሱ ሌላ ጥያቄዎችን እያነሱ እራሳቸው መመለሱን ተያይዘውታል፡፡
ቡርኪናፋሶ ምንም እንኳ እንደ አብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገራት ድሃ ብትሆንም እንደ እኛ 6ና 7 ሚሊዮን ህዝብ አይራብባትም፡፡ ምንም እንኳ እስከ ትናንትና ድረስ በመፈንቅለ መንግስት ስልጣን ላይ የተቆናጠጠ መሪ ያስተዳድራት የነበር ቢሆንም ፓርቲዎችና ህዝቡ ሀሳቡን የሚያንጸባርቅባቸው ሚዲያዎችና ሌሎች ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ዘርግታለች፡፡ ገና እ.ኤ.አ በ1990 ጀምሮ ሬድዮና ቴሌቪዥንን በግል በመያዛቸው ህዝቡ ለአማራጭ ሚዲያ ቅርብ ነው፡፡ ኢንተርኔት ኢትዮጵያ ውስጥ እንደሚደረገው በስርዓቱ አይታፈንም፡፡ ቡርኪናፋሶ እንደ ኢትዮጵያ ጋዜጠኞች በጅምላ እስር ቤት የሚታጎሩባት፣ በገዥው ፓርቲ ጫና የሚሰደዱባት፣ ሚዲያዎች የሚታፈኑባትና የሚዘጉባት አገር አይደለችም፡፡
ባለፉት አመታት ለአጭር ጊዜ ከሶስት የማይበልጡ ጋዜጠኞች ታስረዋል፡፡ ባለፉት 20 አመታት በሚዲያው ታሪክ አስከፊው የሚባለው የአንድ ጋዜጠኛ ባልታወቁ ሰዎች መገደል ብቻ ነው፡፡ በቡርኪናፋሶ ያለፉት 20 አመታት ታሪክ ውስጥ በሚዲያው ጠባሳ ነጥብ ተደርጎ የሚወሰደውና የውጭ ተቋማት ጫና ለማሳደር የሚጥሩበት ጉዳይም የዚህ ጋዜጠኛ ሞት ነው፡፡ ከአምስት አመት በፊት አንድ ጋዜጠኛ የ‹‹እንገድልሃለን›› ማስፈራሪያ ስለደረሰበት ዓለም አቀፍ የጋዜጠኛ ማህበራት አሁንም ድረስ ስርዓቱን በመውቀሻነት ይጠቀሙበታል፡፡ በቡርኪና ፋሶ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብሰባ እንዳያደርጉ፣ ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይወጡ አይከለከሉም፡፡ የአገሪቱ ሲቪክ ማህበራት ኢህአዴግ መራሹ ‹‹መንግስት›› ስር ካሉት የተለዩ ናቸው፡፡ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በሽብር ስም ወህኒ አይወረወሩም፡፡ በአጭሩ ቡርኪናፋሶ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚጠየቁትን አብዛኛዎቹን የፖለቲካ ጥያቄዎች መልሳለች፡፡
ምንም እንኳ ቡርኪናፋሶ ከእኛ የተሻለ፣ እኛ የምጠይቀውን ጥያቄ የመለሰች ቢሆንም፣ ፖለቲካዊ ስርዓት ብትገነባም በሚፈለገው መንገድ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ሰፍኖበታል ለማለት ግን አያስደፍርም፡፡ ቡርኪናፋሶን ለባለፉት 27 አመታት ያስተዳደሩት ፕሬዝደንት ብላይሴ ኮምፓሬ ወደ ስልጣን የመጡት ተወዳጁን የቀድሞ የአገሪቱን ፕሬዝደንት ቶማስ ሳንካራን አስገድለው ነው፡፡ የገዳዮቹ ቻርለስ ቴለርና ሙአመድ ጋዳፊ የቅርብ ጓደኛም እንደመሆናቸው ለህዝቡ ምቹ ናቸው ማለት አይቻልም፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሶሻሊስት ከነበረው ቶማስ ሳንካራ የተለየ ሆነው በመገኘታቸው የምዕራባውያን ተላላኪ ሆነው አገልግለዋል፡፡ በተለይ የምዕራብ አፍሪካን አለመረጋጋት ለመቆጣጠር ፈረንሳይና አሜሪካ ቡርኪናፋሶን ተጠቅመውበታል፡፡
እ.ኤ.አ በ1991፣ በ1998፣ በ2005ና 2010 በተደረገው ምርጫ አሸነፍኩ ቢሉም ያልተዋጠላቸው በርካቶች እንደነበሩ ይነገራል፡፡ በፕሬዝዳንትነቱና በፓርቲያቸው ደስተኛ ያልሆኑት ቡርኪናፋሶውያን እ.ኤ.አ በ2011 በርካታ አመጾችን አስነስተው ስርዓቱን አስደንግጠዋል፡፡ ለአብነት ያህል በዚሁ አመት ሰራዊቱ ደሞዜ አልተከፈለኝም ብሎ የጀመረው አመጽ ፕሬዝደንቱ ወደ ተወለዱበት መንደር እንዲደበቁ አስገድዷቸው ነበር፡፡ የህገ መንግስቱ መሻሻል ሀሳብ የቀረበው ከአመት በፊት ሲሆን ተቃሞው ገጥሞት እንደገና ተቋርጦ ቆይቷል፡፡
ከእኛ አገር የተሻለ ግን ደግሞ መሻሻል በነበረበት የቡርኪናፋሶ ዴሞክራሲ ውስጥ ህዝቡ ጥያቄውን ሲያቀርብ ቆይቶ ሰሞኑን አቅሙን አሳይቷል፡፡ ቶማስ ሳንካራን ያህል ተወዳጅ መሪ አስገድለው ስልጣን ላይ የወጡትን ፕሬዝዳንት በሰዓታት ውስጥ ማፍረክረክ ችሏል፡፡ የገዥው ፓርቲ ዋና ጽ/ቤት፣ ቴሊቪዥን ጣቢያው፣ ፓርላማው፣ የባለስልጣናትን ቤትና ሌሎችም የመንግስት ቢሮዎች በመቆጣጠርና በእሳት በማጋየት የጀመረው የተቃውሞው ጎራ የአንድ ቀን ውሎ ህገ መንግስቱን በማሻሻል ስልጣናቸውን ለማራዘም ደፋ ቀና ሲሉ የነበሩት ፕሬዝዳንት ‹‹መንግስትን አፍርሸዋለሁ፡፡ መልዕክቶቻችሁን ሰምቻለሁ፡፡ የሽግግር መንግስት ይቋቋማል›› ብለው የተለየ አቋም እንዲይዙ አስገድዷቸዋል፡፡ ከዛ በፊት ብዙም ቁብ ሰጥተዋቸው ያልነበሩትን ተቃዋሚዎች ‹‹አመጹን እንድታቆሙ እለምናለሁ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ከሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች ጋር በመወያየት ችግሩን መፍታት አለብን›› ብለው እንዲማጸኑ ግድ ሆኖባቸዋል፡፡ በስተመጨረሻም በአንድ ቀን የህዝብ አመጽ ስልጣን መልቅቃቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
በቡርኪናፋሶው ገዥ ፓርቲ ላይ የተነሳው አመጽ ሰራዊቱንም ጭምር ያሰባሰበ ሲሆን ቀድሞው የጦር ሚኒስትር ጀኔራል ኩአሜ ሎውጉን ጨምሮ በርካቶች ሰላማዊ ታጋዮችን ተቀላቅለዋል፡፡ ፓርላማ፣ የመንግስት መስሪያ ቤቶችንና የባለስልጣናቱን ቤት ባነደደው እንቅስቃሴ የሞቱት ሰዎች ጥቂቶች እንደሆነ የታወቀ ሲሆን ይህም መከላከያና፣ ፖሊስና ደህንነቱ ከህዝብ ጎን እንደቆመ በግልጽ አሳይቷል፡፡
ከኡጋዱጉ ወደ አዲስ አበባ?
የአረቡ የጸደይ አብዮት በተነሳበት ወቅት ጂቡቲ፣ ሱዳን፣ ዚምባብዌ፣ ማዕከላዊ አፍሪካና ሌሎችም አምባገነኖች ስልጣን ላይ የተቆናጠጡባቸው አገራት ውስጥ ጅምር እንቅስቃሴዎች ተስተውለው ነበር፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ደግሞ ምንም አይነት እንቅስቃሴ

Sunday, November 2, 2014

Burkina Faso: A warning to other African leaders

NAIROBI – Violent clashes in Burkina Faso that led to the overthrow of the president are a stark warning to other African leaders pushing constitutional change to hang on to power, analysts say.

Chaos in Burkina Faso erupted this week as lawmakers prepared to vote to allow 63-year-old Blaise Compaore — who took power in a 1987 coup — to contest elections in November 2015.
While Compaore was forced out Friday, Burkina Faso is far from alone in having a president reluctant to relinquish office.
“It is a warning both to ageing regimes and for those trying to stay in power beyond constitutional limits,” said Thierry Vircoulon of the International Crisis Group (ICG).
“During the Arab Spring the question was whether Africa will have its own spring? Perhaps the attempts to change the constitutions will lead to it now.”
Countries including Benin, Burundi, Congo-Brazzaville, the Democratic Republic of Congo and Rwanda are all reportedly pondering change to allow their leaders a third term.
But the impact of events in Ouagadougou, and the storming of its parliament, may give several leaders across the continent “pause for thought”, said Paul Melly from Britain’s Chatham House.
“Burkina Faso has demonstrated that in today’s Africa popular acquiescence cannot be taken for granted,” Melly said.
– ‘Wake-up call for presidents’ –
Burkina Faso is far from the first country where heads of state seeking to extend their rule have been challenged.
In Niger, Mamadou Tandja was ousted by the army in 2010 after a third-term bid, while in contrast, Senegal’s President Abdoulaye Wade lost 2012 elections despite winning constitutional permission to run three times.
Some have carried it off. Cameroon’s Paul Biya, in power since 1982, successfully changed laws for another term in 2011, but the strongman had ensured the opposition was quashed.
Other nations were laws have been tinkered with to the benefit of their leaders include Algeria, Angola, Chad, Djibouti and Uganda.
But events in Ouagadougou may ring alarm bells for others.
“The evolving situation in Burkina Faso will hopefully serve as a wake-up call for presidents who are considering tailoring the constitution to suit their own interests, in west Africa and beyond,” said David Zounmenou, from the South African-based Institute for Security Studies (ISS).
And while the African Union sanctions those who make constitutional changes for the purpose of staying in power, such threats have had little impact, Zounmenou added.

Saturday, November 1, 2014

Eight Ethiopian Air Force Pilots Defected In October

A total of eight Ethiopian Air Force pilots have defected this month, according to a senior Eritrean official.
The official didn’t specify if the pilots defected to Eritrea, or if they managed to flee the country with their aircrafts, though it is highly likely they did in both cases.
The defections come as reports indicate the Ethiopian Air Force is in shambles, and that the TPLF oligarchs are “disgusted” by their poor performances.
Ethiopia is no stranger to high-profile air force defections. Last year, four Ethiopian helicopter pilots and a MiG-23 pilot defected to Eritrea.
The names of the helicopter pilots are Cap. Aklilu Mezene, Cap. Tilahun Tufa, Cap. Getu Worku and Cap. Biniam Gizaw, while the name of the MiG-23 pilot is Daniel Yeshewas.
Source: madote.com