Search This Blog

Saturday, August 9, 2014

ጥያቄው የጉልቻ መለዋወጥ ሳይሆን የለውጥና የነጻነት ነው

ለለውጥ እንጩህ !!! ነፃነታችን በጃችን ላይ ነው፡፤ !!!
ለውጣችንን እና ነጻነታችንን ያፈኑብንን አምባገነን ፖለቲከኞች ድባቅ የመምታት የዜግነት ግዴታ አለብን !!!
አዎ የኛ የኢትዮጵያውያን ጥያቄ የግለሰቦች በስልጣን ወንበር ላይ መፈራረቅ ሳይሆን ጥያቂያችን የለውጥ ጥያቄ ነው። የፖለቲካ አስተዳደር ለውጥ የኑሮ ውድነት የሚያላቅቅ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ለውጥ በጋራ ህብረተሰባዊነት ላይ የተመሰረት የማህበራዊ ፍትህ እኩልነት ለውጥ የነጻነት እና የመብት ማግኘት ጥያቄ በሃገራችን ተዘዋውረን በፈለግነው ቦታ የመስራት እና የመኖር ጥያቄ የመሳሰሉት ለውጦች በሃገራችን ላይ የሃገራችን ባለቤቶች ስንሆን የ ሚገኘው ብልጽግና እና እድገት ባለቤት መሆናችንን የሚያረጋግጥልን ለውጥ እንፈልጋለን፡፡
የጉልቻ መለዋወጥ ከሆነ እንደ ለውጥ የሚታየው በኢትዮጵያውያን የ እለት ከእለት የሕይወት ሂደት ውስጥ ድህነት እና ነጻነት ማጣት እንጂ ምንም አይነት የፈየደው ነገር አለመኖሩን ከሃይለስላሴ ጀምሮ ያየነው ነው፤ መንግስቱ ሓ/ማርያም መጣ ሄደ መለስ ዜናዊ መጣ ሄደ አሁንም ጠቅላይ ተብሎ ተሾመልን ይህም ጉልቻውን ለፖለቲካ ማጣፈጫ ሆነ እንጂ እንኳን ሊያስተዳድረን ይቅር እና የገዛ አንገቱን እንኳን ማዘዝ አልቻለም፤ ታዲአ የዜጎችን የለውጥ ጥያቄ ጉልቻ በመለዋወጥ መመለስ እንደማይቻል በይፋ እያየነው ነው፡፡
የኛ የለውጥ ጥያቄ የህዝቦችን የዜግነት መብቶች የሚያረጋግጥ እንጂ በውጭው አለም እና በሃገር ውስጥ ብሄራዊ ውርደት የሚያከናንብ አስተዳደር አይደለም፤ የኛ የለውጥ ጥያቄ በተስኪያናችንን እና መስኪዳችን እንዲሁም ታሪኮቻችንን የሚያረክስ የፖሊስ እና የጦር ሰራዊት ለውጥ ሳይሆን የነጻነት እና የመብት ጥያቂያችንን በህገመንግስት መሰረት የሚያስከብርልን አስተዳድር ነው፤ የኛ የለውጥ ጥያቄ በኑሮ ውድነት አደባይቶን በሙስና ጥቂት ሃብታም ብዙ ደሃ የሚፈጥር ዋሾ አስተዳደር አይደለም፡፤ የኛ የለውጥ ጥያቄ ህዝባዊ መሰረት ያለው ሚዲያ እንጂ በግምት የሚደሰኩር ውሸታም ሚዲያ አይደለም፡፤በአጠቃላይ የለውጥ ጥያቄያችን የባሰ እና የበሰበሰ መንግስት እንዲያስተዳድረን ሳይሆን እንደ ሃገር ባለቤትነታችን መብታችንን አስከብሮ በነጻነታችን እያኖረ ሃገራዊ ሃላፊነት እና ግዴታ እንዲሰማን የሚያደርግ መንግስት እንጂ የጉልቻ ተፈራራቂ አምባገነን ንግስና አይደለም፡፡
ኢትዮጵያውያን ለውጥ እንፈልጋለን ስንል የለውጥ ጥያቂያችንን መከለያ አድርጎ የስልጣን ጥሙን የሚያረካ የፖለቲካ ድርጅት እና የፖለቲካ ወያላ አንፈልግም፡፤ የኛን የለውጥ ጥያቄ ለፖለቲካ አጀንዳቸው ተጠቅመው ነጻነታችንን የሚያስነጥቁን የፖለቲካ ድርጅቶችን አንናፍቅም፡፤እኛ በፈረንጅ ቋንቋ የተገነባ የዲሞክራሲ ንግድ በነጻነታችን ላይ እንዲሰራፋ አንፈልግም። ኢትዮጵያውያን ነጻነታችን ያለው በፈረንጆች ሳይሆን በ እጃችን ላይ ስለሆነ እያንዳንዳችን ነጻነታችንን ለማስመለስ መረባረብ ግድ ይለናል። ጥያቂያችን የምእራብ ዲሞክራሲ ሳይሆን በነጻነት የመኖር ትያቄ ነው፡፤ ለለውጥ አሁንም እንጮሃለን። ፈረንጅ ለራሱ አጽድቆ ያራባውን ዲሞክራሲ ከነጻነት በኋላ እንደርስበታለን።
የዲሞክራሲ ትርጉም ቢገባንም ገዢዎቻችን ግን ለለበታ ስለሚጠቀሙበት በቋንቋችን ነጻነት ለውጥ እያልን እንዘምራለን፡፤ለለውጥ በጋራ በመነሳት ነጻነታችንን በትግላችን መቀናጀት ግድ ይለናል። በሃገራችን እና በነጻንትችን ላይ ባለቤቶች እንደሆንን ሃላፊነት ሊሰማን ስለሚገባ ነጻነታችንን ራሳችን ማረጋገጥ አለብን እንጂ የማንም ችሮታ እንዳልሆነ ተገንዝበን በጋራ ለለውጥ መነሳት ግዲታችን ነው። ነጻነታችን በ እጃችን ስለሆነ ዛሪውኑ ለማስመለስ እንትጋ።

No comments:

Post a Comment