Search This Blog

Monday, March 31, 2014

አምባገነናዊውን ስርዓት አቅፈውና ደግፈው የያዙት ምዕራባዊ አገራት

በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ጭቆና፣ ስቃይ እና መከራ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እና ተጠናክሮ እንዲቀጥል ካደረጉት ምክንያቶች መካክል አንዱ፣ የወያኔ መንግስት ከምዕራባዊያን የሚያገኘው ያልተቋረጠ ድጋፍ እና ሙገሳ ትልቅ ቦታ ይይዛል። ከነዚህ መንግስታት የሚያገኘው ድጋፍ እና ሙገሳ ምክንያት የማን አለብኝነት ስሜት ስርዓቱ እንዲሰማውና የኢዴሞክራሲያዊ ስርዓት በህዝቡ ላይ እንዲንያሰራፉ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። ስርዓቱም ከነችግሩ ለረዥም ጊዜ በስልጣን እንዲቆይ ካደረጉት ምክንያቶች መካከል የምዕራባዊያን ድጋፍ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። እነዚህ ሀገራት የራሳቸውን ብሄራዊ ጥቅም ብቻ ትኩረት በመስጠታቸው ላለፉት 25 ዓመታት የኢትዮጵያ ህዝብ በጭቆና ውስጥ እንዲያሳልፍ አድረገውታል። የሀገሪቱ መልካምድር\ጅኦግራፍያዊ አቀማመጥ፣ የመንግስት ለምዕራባዊያን ፍላጎት አጎብዳጅነት እና ሃገሪቱ በአካባቢው ብሎም በአፍሪካ ፖለቲካ ያላት ማእከላዊ ስፍራ የለጋሽ ሀገራትን ትኩረት ሊስብ ችሏል። በዚህ ምክንያት ምዕራባዊያን የወያኔ ስርዓትን አቅፈውና ደግፈው በመያያዛቸው ህዝቡ ከዚህ አስከፊ ስርዓት ነጻ ለመውጣት የሚያደርገውን ትግል አስቸጋሪ አድርጎታል።
The world have to see the truth about dictatorial regime weyanee
የወያኔ መንግስት በህዝብ ላይ እያደረሰ ካለው ዘርፈ ብዙ ወንጀሎች እና የስርዓቱ ልዩ መለያ ባህርያት መካከል በዋናነት፣ በሀይል ህዝቦችን ለዘመናት ከሚኖሩበት መሬት ማፈናቀል እና መሬታቸውንም በርካሽ በኢንቨስትመንት ስም መቸብቸብ፤ የጸረ-ሽብር ህግ በማውጣት የፖለቲካ አመራሮችን እና ጋዜጠኞችን ማፈን፤ ከፍተኛ ሙስና እነዲሁም ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በማስገባት የስልክ እና የኢንተርኔት ክትትል እና ጠለፋ ማድረግ ተጠቃሽ ናቸው። የምዕራባዊያን በወያኔ ላይ ያላቸው ቸልተኝነትና ለዘብተኛ አቋም መንግስት የማናለብኝነት ስሜት እንዲሰማውና በህዝብ ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃና ተግባር ከጊዜ ወደ ጊዜ መጠኑና ስፋቱን እየጨመረ በመሄድ የሀገሪቱን ብሎም የአካባቢውን መጻይ ዕድል አሳሳቢ አድርጎታል።
ከምዕራባዊያን የሚገኝ እረዳታ በመጠቀም ብዙ የአፍሪካ መንግስታት አምባገነናዊ ስርዓትን በሰፊዊ የማጠናከራቸው ሁኔታ አዲስ ነገር አይደለም። ከሰሞኑም የወጣው የHuman Rights Watch ሪፖርት እንዳመለከተው መንግስት ህዝቡን እንዴት ጠፍንጎ እና ጨቁኖ እንደያዘው ምናልባት ለውጭ ማህበረሰብ አዲስ ነገር ሊመስል ቢችልም ለኢትዮጵያ ህዝብ ግን አዲስ አይደለም። በተለያዩ ወቅቶች የተቃዋሚ ሓይሎች፣ ጋዜጠኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ሲገልጹት የቆዩት ጉዳይ ነው። ነገር ግን እዚህ ላይ መጠቆም የሚገባን፤ ወቅታዊ ሪፖርቶችን በተከታታይ በማቅረብ፣ ሰፋ ያለ ማብራሪያና መረጃወችን የሚያቀርበውን የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት( Human Right Watch) ማመስገን ይገባናል።

የሌቦች ማምረቻ የሆነው የወያኔ መንግስት ጨረታ ሲጋለጥ

የመንግስት ባለስልጣናት የሙስና መንገዳቸውን ለማሳካት ሲሉ በመንግሥት ፖሊሲ፣ አሠራርና መመርያ ላይ ጫና እየፈጠሩ እንደሚመቻቸው ተደርጎ እንዲወጣ በማድረግ ላይ ናቸው ሲል ሙስና ኮሚሽን አማሯል።
ኢትየጵያ ውስጥ አሁን ያለው የሙስና መጠን ትናንትና ከነበረው እጥፍና ከእጥፍ በላይ አሻቅቧል፡፡ አሁን አገሪቷ ውስጥ ያለው የኑሮ ውድነት ወደላይ እንዲያሻቅብ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱም የሙስና ጣርያ መንካት ነው፡፡ በዚህ ደረጃ ላይ አሳሳቢ መሆኑን መግለጽ ቀርቶ የእገሌን አገር ደረጃ አያክልም የሚለውን አባባል የኢትዮጵያ ሕዝብን እንደመናቅ ይቆጠራል፡፡በአሁኑ ወቅት ሙስና በኢትዮጵያ ውስጥ ተንሰራፍቷል፡፡ ባለጉዳይም ጉቦ ካልሰጠ ጉዳዩን እንደማያስጨርስ፤ ጉዳይ ፈጻሚም ገንዘብ ካላገኘ ጉዳይን ማስጨረስ የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን በገሃድ በሚታይበት ደረጃ ላይ ነን፡፡ በቀበሌ፣ በወረዳ፣ በክፍለ ከተማ፣ በአዲስ አበባ መስተዳድር፣ በፖሊስ፣ በፍርድ ቤት፣ በአገር ውስጥ ገቢ፣ በጉምሩክ፣ በመንገድ ትራንስፖርት፣ በሆስፒታሎች፣ በኢሚግሬሽን፣ ወዘተ ጉዳይን ለማስጨረስ ጉቦ መስጠት የተለመደ ሆኗል፡፡
corrupted weyanee official Bereket simon with the father of corruption & their right hand man Shek Mohamed al amoudi
ጉቦ መስጠትም ሆነ መቀበል እንደ ብቃትና እንደ ሥልጡንነት እየታየ ነው፡፡ ጉቦ የማይቀበል የማይረባና የማይጠቅም ተብሎ የሚሰየምበት ደረጃ ላይ መድረሳችንን እያንዳንዱ ሰው በሚገባ ያውቀዋል፡፡ እንደዚህ በመሰለ አስፈሪ ሁኔታ ውስጥ ባለንበት ወቅት ሙስና ኢትዮጵያ ውስጥ አሳሳቢ ደረጃ ላይ አይደለም ሲባል ምን ማለት ነው? መረጃው የተገኘውስ ከየት ነው? ከተበዳይ ወይስ ከበዳይ?
ኢትዮጵያ ውስጥ የሚካሄዱ የአገር ውስጥና የውጭ አገር ግዢዎች አነስተኛም ይሁኑ ትላልቅ የፕሮጀክት ጨረታዎች ያለኮሚሽን ክፍያ የተፈጸሙ ናቸው የሚል ጥናት ፍፁም ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም፡፡ ምንልክሳልሳዊበአሁኑ ወቅት በተለያዩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ የሚካሄዱ ግዢዎችና ጨረታዎች ሕጋዊነትን ለማስያዝ ብቻ የሚካሄዱ ካልሆነ በስተቀር፣ አስቀድሞ ከታቀደውና ከታለመው ሰው ወይም ድርጅት ውጭ ማንም እንዲገባ በማይፈቀድበት ደረጃ ላይ መድረሳችንን የዋህ ሰው ሳይቀር በሚገባ የሚረዳበት ደረጃ ላይ እኮ ነን ያለነው፡፡ ግዢዎች ሲፈጸሙ ወይም ጨረታ በሚወጣበት ጊዜ የሚደረገውን ለአብነት እንይ፡፡

በሽብር የተከሰሱት ሙስሊሞች ያቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ አከራከረ

635 የመከላከያ ምስክሮች በተከሣሾች ተቆጥረዋል
በትናንትናው እለት ሙስሊሙ ህብረተሰብ ተቃውሞ አሰምቷል

በአወሊያ ት/ቤት መነሻነት “ድምፃችን ይሠማ” በሚል ከተፈጠረው መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጋር በተያያዘ በእነ አቡ በከር መሃመድ መዝገብ ስር፣ በሽብር ወንጀል የተከሰሱት 18 ግለሰቦች ያቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ ጭብጥ ከትናንት በስቲያ ፍ/ቤቱን አከራክሯል፡፡ 
የተለያዩ የሽብር ተግባሮች ውስጥ ተሳትፈዋል ተብለው ክስ የቀረበባቸው 18 ተከሳሾች፣ ቀደም ሲል በአቃቤ ህግ የቀረበባቸውን ማስረጃ ይከላከሉ ሲል ፍ/ቤት ብይን መስጠቱን ተከትሎ ይከላከሉልናል ያላቸውን 635 የሰው ምስክሮች ቆጥረዋል፡፡ 
በትናንት በስቲያው ችሎት ተከሳሾች በጠበቆች አማካይነት ከቀረቡት የመከላከያ ማስረጃ ጭብጥ ውስጥ አቃቤ ህግ የሚቃወማቸውን ነጥቦች በዝርዝር ጠቅሶ አቅርቧል፡፡ ከተጠቀሱት የመከላከያ ማስረጃ ጭብጦች መካከልም “ሃይማኖታዊ ቃላትን የሃይማኖት አባቶችን አቅርበን እናስተነትናለን” ማለታቸው  ፍ/ቤቱን በስፋት አከራክሯል፡፡ 

ቀደም ሲል በአቃቤ ህግ የማስረጃ አቀራረብ ወቅት ሲጠቀሱ ነበር ከተባሉት ሰደቃ፣ ጅሃድ፣ አዛን፣ አህባሽ እና ሌሎችም ሃይማኖታዊ ትርጉም አላቸው ለተባሉ ቃላት ሙያዊ ትንታኔ እናሰጥበታለን መባሉን የተቃወመው አቃቤ ህግ፤ “የእነዚህ ቃላት ትርጓሜና ትንታኔ የሚቀርብበት ምክንያት የለም፣ በዚህ ችሎት እየታየ ካለው ጉዳይ ጋርም አይገናኝም“ ሲል አመልክቷል፡፡ ፍ/ቤቱም በማጣሪያ ጥያቄው እነዚህን ቃላት ለማስተንተን ሙያዊ ማስረጃ ማቅረብ ለምን ያስፈልጋል ሲል የጠየቀ ሲሆን የተከሳሽ ጠበቆች በሰጡት ምላሽ፤ ቀደም ሲል አቃቤ ህግ ማስረጃውን ሲያቀርብ “አህባሽ የሚባል ሃይማኖት የለም” በማለቱ ሃይማኖቱ መኖሩን ለማስረዳት፣ ወሃቢያን በቀጥታ ከሽብርተኝነት ጋር አያይዞ በማስረዳቱ ስለወሃብያ ምንነት ለማስረዳት፣ አዛን በማይደረግበት ጊዜ አዛን አድርገው ህዝቡን ቀስቅሰዋል በማለቱ አዛን መቼ እና እንዴት ይደረጋል የሚለውንና ሌሎች ሃይማኖታዊ ትርጓሜ የሚያስፈልጋቸውን ተንትኖ ለማስረዳት መሆኑን አመልክተዋል፡፡ እነዚህን ቃላት ሽፋን አድርገው ወንጀል ፈፅመዋል ስለተባለም ትክክለኛ ፍቺውን ለማስገንዘብ ነው ብለዋል፡፡ 

Sunday, March 30, 2014

ፍትሕ ማግኘት ገጠመኝ ሙስና ደግሞ የአንቀጾች ሁሉ የበላይ አንቀጽ እየሆነ መጥቷል

የበደለ፣ የአገር ሀብት ያባከነ፣ ሕገ የረገጠ ግለሰብ ማጥፋቱ እየታወቀ ይቀጣል ወይስ አይቀጣም ለሚለው ጥያቄ ወሳኙ ማስረጃ መሆኑ እየቀረ ነው፡፡
የፖለቲካ ገጠመኝ ሆኗል፡፡ ይታሰራል የተባለው ሊሾም፣ ተጠያቂ ይሆናል የተባለው ጠያቂ የሚሆንበት ሁኔታ አለ፡፡
መልካም አስተዳደር በሕግና በመርህ ደረጃ መከበር አለበት ተብሎ የታወጀ፣ የተነገረ፣ የተለፈፈለት ነው፡፡ በተግባር ደግሞ አቤት ብዬ ሰሚ አገኛለሁ፣ ቅሬታ አቅርቤ ይፈታልኛል የሚል ዜጋ የለም!!!! በዚህ ዙሪያም ጉቦና ጥቅማ ጥቅም የበላይነት እየያዙ ነው፡፡ የአቅም ማነስ ችግር ትልቅ እንቅፋት ነው፡፡ ስብሰባዎችና ሥልጠናዎች የችግር መፍቻ መድረኮች መሆናቸው ቀርቶ መደበቂያ እየሆኑ ነው፡፡ ‹‹በስብሰባና በሥልጠና ምክንያት ኃላፊ የለም›› የሚል ማስታወቂያ መለጠፍ ነው የቀረው፡፡ ኃላፊ ቢሮው ገብቶ አቤቱታ አንብቦ ችግር መፍታት መርህና ግዴታው መሆኑ ቀርቶ የፖለቲካ ገጠመኝ እየሆነ ነው፡፡
የሕግ የበላይነት እንዲኖር፣ ሰብዓዊ መብት እንዲከበር፣ የፕሬስ ነፃነት እንዲረጋገጥ፣ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት እውን እንዲሆን የሚያደርጉ ሕገ መንግሥትና ሕጎች አሉን ????????? ከድህነት የሚያላቅቅ፣ መካከለኛ ገቢ ወዳላት አገር የሚያሸጋግር፣ የቤት፣ የጤና፣ የትምህርት፣ የትራንስፖርት፣ ወዘተ ችግሮችን የሚፈታ ዕቅድም አለን ???????????
እነዚህ አሉ ማለት ግን ዲሞክራሲ ተረጋገጠ፣ ልማት እውን ሆነ ማለት አይደለም፡፡ በመርህ ደረጃ ተግባር ላይ ካዋልናቸው ይጠቅማሉ፡፡
ካላከበርናቸው፣ ከረገጥናቸውና ከጣልናቸው ደግሞ ገጠመኝ ይሆናሉ፡፡ ፍትሕ ገጠመኝ እየሆነ ነው፡፡ምንሊክሳልሳዊ የፍትሕ መጓደል በሚያሳስብ ሁኔታ እየታየ ነው፡፡ በፍትሕ አካላት ውስጥ በአቅምና በአመለካከት ድክመት አለ፡፡ የሥነ ምግባር ጉድለት በትልቁ እየታየ ነው፡፡ በጠበቆች፣ በዳኞችና በዓቃቢያነ ሕግ በኩል አሳሳቢ የሥነ ምግባርና የአቅም ችግር እየተስተዋለ ነው፡፡
በአጠቃላይ የፍትሕ አካላት መጠናከር እያሳዩ ከመጓዝ ይልቅ እየተልፈሰፈሱና እየተንገዳገዱ ናቸው፡፡ በዚህ ምክንያት ፍትሕ ማግኘት መርህ መሆኑ ቀርቶ ገጠመኝ እየሆነ ነው፡፡ ጉቦ የአንቀጾች ሁሉ የበላይ አንቀጽ እየሆነ መጥቷል፡፡ሰላማችን፣ ሉዓላዊነታችን፣ አንድነታችንና ህልውናችን በመርህ ደረጃ ዋስትና ያላቸው መሆናቸው ቀርቶ የፖለቲካ ገጠመኝ ሆነዋል፡፡ የአገር እና የህዝብ ህልውና ገጠመኝ በመሆኑ ወያነ ደግሞ የዛፍ ላይ እንቅልፍ ተኝቷል፡፡ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም በጋራ የዛፍ ላይ እንቅልፉን የሚለጥጠውን ወያነን በማውረድ ህዝባዊ የበላይነትን መቀናጀት የዜግነት ግደታችንን መወጣት አለብን::

Saturday, March 29, 2014

Welcome to Stasi-opia: The Stasi-zation of Ethiopia under TPLF/EPRDF rule

Over the last two-decades the people of Ethiopia under the TPLF/EPRDF rule have endured the reign of terror, fear, and propaganda horrifyingly reminiscent of the notorious Ministry of State Security known as the Stasi in the former German Democratic Republic (GDR).1 It is within recent memory that the Stasi security and surveillance campaign kept citizens of East Germany under a constant reign of fear and terror until the fall of the Berlin Wall on November 9, 1989. Totalitarian control of citizens throughout history has left a tragic mark in the collective psyche of humanity. The Stasi, Gestapo, KGB, Benito Mussolini’s OVRA, and many others, all of these brutal institutions committed heinous act of terror against innocent citizens.
Ethiopian government is spying on its citizensThe uncomfortable truth is that we are not even talking in past tense term about the horror and repression of citizens in our world. In fact, such organized and government-led criminal and terrorist enterprises continueto function in the 21st century world. Among several of such regimes in the world today, one in particular stands out on the spectrum of totalitarian index. With its full-fledged infrastructure of security and surveillance machinery, the TPLF/EPRDF-led regime in Ethiopia has time and again demonstrated that its league is not with those who envision freedom and justice but with those who rule by fear and terror.

ወያኔ የእምነት ተቋማትን በጥብቅ የሚቆጣጠርበት ህግ ሊያጸድቅ ነው ህጉ ጣጣ እንዳያመጣ የሰጉ ኢህአዴግን እየመከሩ ነው

ኢትዮጵያን ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ እየገዛ ያለው ወያኔ የሃይማኖት ተቋማትንና ምዕመናኑን በጥብቅ የሚቆጣጠርበትን ህግ ለማጽደቅ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተሰማ። የህጉ ረቂቅ የደረሳቸው ከፍተኛ ዲፕሎማቶች ኢህአዴግን አበክረው እየመከሩና በሚያመጣው አጠቃላይ መዘዝ ዙሪያ እያስጠነቀቁ ነው።
ጎልጉል ከዲፕሎማት ምንጮቹ ባገኘው መረጃ መሰረት ኢህአዴግ በእምነት ተቋማት ላይ ቁጥጥሩን የሚያጠብቅበትንና ከሃይማኖት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውጭ መሰብሰብን፣ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግንና የተቃውሞ ድምጽ ማሰማትን የሚከለክል ህግ አዘጋጅቷል።
የዜናው ምንጮች ዝርዝር ህጉን ለጊዜው ይፋ ከማድረግ እንደሚቆጠቡ አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ የሚደነገገውን አዲስ ህግ ጥሰዋል በሚል የሚከሰሱ ምዕመኖች እስከ እድሜ ልክ በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ የሚያዝ አንቀጽ አለበት። አዲሱ ህግ ከሽብርተኞች ህግ ጋር የሚጣቀስ እንደሆነም የጠቆሙት ክፍሎች ኢህአዴግ “ከእምነት ነጻነት” ጥያቄ ጋር በተያያዘና በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ውስጥ ውስጡን እየነደደ ያለው ችግር ስላስጨነቀው ይህንን ህግ ለማውጣት መገደዱን አስረድተዋል። በሌላ በኩልም እስካሁን መፍትሔ ያላገኘው የሙስሊሞች ጥያቄ ከዚያም ጋር ተከትሎ የተከሰተው ደም መፋሰስ ወደፊት ሊያመጣ በሚችለው ጉዳይ ላይ ኢህአዴግን በብርቱ አሳስቦታል፡፡
ኢህአዴግ ከቀን ወደ ቀን ቀውስ እየተደራረበት እንደሆነ የተረዳችው አሜሪካ በከፍተኛ ባለስልጣኖቿ አማካይነት ኢህአዴግን እየመከረች እንደሆነ ከዲፕሎማቶች የተገኘው መረጃ ያመለክታል። ከፖለቲካው ቀውስና በቀጠናው ካለው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ አሜሪካ በተደጋጋሚ የህወሃትን ሰዎች በተናጠል እያነጋገረች እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል። ዲፕሎማቶቹ እንደሚሉት አሜሪካ መለስ “ከተሰዉ” በኋላ አገሪቱን ማን እየመራት እንደሆነ በቅጡ ለመረዳት በሚያስቸግር ሁኔታ የስልጣን መዛነፍና ደረጃን የጠበቀ የስልጣን ተዋረድ አለመኖሩም አሳስቧታል። ኢህአዴግ ለህልውናዬ ያሰጋኛል በሚል መንግሥታዊ ባልሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች /መያዶች/ ላይ ያወጣውን አፋኝ ህግም ጠቅሰዋል። ዲፕሎማቶቹ በጉዳዩ ዙሪያ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት ወቅቱ አሁን እንዳልሆነ አመልክተዋል።

Friday, March 28, 2014

በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ደማቅ የተቃውሞ ትእይንት ተደረገ

በአዲስ አበባ ታላቁ አንዋር መስኪድን ጨምሮ በተለያዩ የሃገሪቱ ዋናዋና ከተሞች ‹‹ሰላታችንን በመስጂዳችን!›› በሚል መሪ ቃል ህዝበ ሙስሊሙ እያካሄደው ያለው መስጂድ ተኮር የዘመቻ እንቅስቃሴ አካል የሆነው እና የዘመቻው ማጠናቀቂያ የጁምኣ የተቃውሞ ትእይንት በደመቀ መልኩ ተካሂዷል::
ህዝቡን ከመስጂዱ ለመነጠል በመንግስት በኩል እየተሰራ ያለውን ህገ ወጥና ኢ-ህገ መንግስታዊ ስራም ለራሱ ተረድቶ ላልሰሙት ሁሉ በማሰማትና መስጂዶቹን በዒባዳ በማድመቅ ላይ ነው የሚገኘው፡፡ ይህ ወቅታዊና አንገብጋቢ የመስጂድ ባለቤትነትን የማረጋገጥ እንቅስቃሴ የመንግስትን እና የመጅሊስን ሴረኞች እንቅልፍ ማሳጣቱንም ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚመጡ የውስጥ መረጃዎች እያጋለጡ ነው፡፡ ‹‹ሰላታችንን በመስጂዳችን!››ዘመቻ የዛሬው ጁሙአ ድረስ ቀጥሎ የቆየ ሲሆን በአዲስ አበባና በተመረጡ የክልል መስጂዶች ላይም አስቀድሞ የነበሩንን ቋሚ ትዝታ ጥለው ያለፉ ግዙፍ ተቃውሞዎችን በሚያስታውስ መልኩ የደመቀ የተቃውሞ ስነስርአት በማድረግ በሰላማዊ ሁኔታ ዘመቻው መጠናቀቁ ታውቋል::
በዚህም መሰረት ከቀኑ ስድሰት ጀምሮ በአዲስ ወደ አዲስ አበባ አንዋር መስኪድ እና በተለያዩ ከተሞች በሚገኙ የተቃውሞ ወደተመረጡ መስኪዶች የተመመው ህዝበ ሙስሊሙ የመስኪዶችን ውስጥ እና ደጅ በመሙላት መስኪዶቹ የራሱ ሃብት መሆናቸውን እና ሙስሊሙ ህዝብ ሰላም ፈላጊ መሆኑን በደመቀ ተቃውሞ ነጭ ምልክቶችን በማውለብለብ ገልጿል::
ህዝበ ሙስሊሙ ዘመቻውን በተሳካ መልኩ በማድረግ ሰላማዊ ተቃውሞውን አሰምቶ ከኮሚቴው ጎን ዛሬም ቃሉን አክብሮ እንደቆመ በማሳየት በሰላም መመለሱን ለማረጋገጥ ተችሏል::

Thursday, March 27, 2014

Arrests and Detentions of Oromo Students in Southern Oromia


Human Rights League of the Horn of Africa (HRLHA) would like to express its deep concern over the safety and fates of Shakiso High School Oromo Students who became victims of discriminate mass arrest and detention in Shakiso Town of Guji Zone in southern Oromia. Around two hundred ethnic Oromo Students have been sent to a jail in the nearby Adola Town, and some have received varying degrees of injuries both from bullets that were shot by the security forces during the interference and by beatings.
Those high school Oromo Students, almost all of whom are juvenile, were arrested and/or picked up at different times from different places including the school compound followinga minor clash between them and ethnic Amhara Students of the same high school. According to information obtained by HRLHA through its correspondents, the clash between the two groups occurred following a provocation by the ethnic Amhara Students in opposition to the singing of the regional anthem in the regional Oromo Language by ethnic Oromo Students during flag raising ceremony at the school based on the rules and regulations provided for by the constitution of the regional state. The ethnic Oromo Students were reporting the incident and filing their complaints with the school administration when the school compound was raided by the federal security forces. Among the ironies surrounding this incident were that: 1). The Federal Security Forces were deployed to interfere in such very minor and localized issues that could easily be dealt with by local administrative bodies and communities including that of the school itself,
Shakiso High School
2). The ethnic Oromo Students, who were the victims of the clash, were discriminately double-victimized while those who triggered the violence were left unquestioned, 3) Not only that such constitutional provisions as a regional anthem that have been in place for close to two decades becomes a subject of dispute, but also those who attempted to exercise such legal provisions were deemed criminals that belong to detention instead of those who contradicted the constitution head on.

Wednesday, March 26, 2014

WEYANEE'S NONSTRATEGIC POLICY CAUSE CONFLICT WITH IN OROMIA

CONFLICT IN NEGELE BORENA

In and around the town Negele Borena there are two ethnic groups; Guji and Borena. The Guji’s want the town’s name be changed to Negele, but the Borena’s want the name of the town to be as it is. And this leads to conflict and as eyewitnesses of the conflict reported to DireTube news from five to ten individuals must have died in the ensuing clash.
It is reported that the main reason behind today’s conflict being some individuals erasing the name ‘Borena’ from some of the town’s government offices. The Zone’s police information desk officer Constable Kila Bifo told DireTube news that the clash started on Monday March 24, 2014 and that they have asked for an additional peace keeping force from Bishoftu.
It is feared that unless some intervention is put in place the conflict might escalate. As Constable Kila Bifo said the town is in the hands of those individuals who created the conflict and that an additional security force hasn’t yet arrived.

Totalovervåking sprer seg i Afrika

Det er ikke bare USA og Storbritannia som driver med storstilt overvåking av privat kommunikasjon. Og i Etiopia misbrukes det i langt større grad.
I en fersk rapport fra Human Rights Watch (HRW) kommer det frem hvordan Etiopia har bygget opp et stort overvåkingssystem for å kontrollere borgernes nett- og telefonbruk.
I landet er det tele- og nettmonopol. Og ifølge HRW er det ingen rettsskranker som hindrer myndighetene fra å få oversikt over hvem som har kontakt med hvem på telefon, sms og internett. I tillegg lagrer de også telefonsamtaler i stor skala. I teorien har myndigheten  mulighet til å lagre alle telefonsamtaler som skjer i landet.
Etiopia får hvert år mangfoldige bistandsmillioner fra Norge. I 2012 fikk Etiopia nesten 230 millioner av Norge, cirka 35 millioner gikk direkte til den etiopiske staten, fordelt på energi/klima og utdanningsprosjekter. 1,5 millioner gikk direkte til Addis Abebas universitets senter for menneskerettigheter.

Får høre samtaler i avhør

Ifølge rapporten skjer det ofte i avhør at politiet spiller av telefonsamtaler som den pågrepne har hatt med familie og venner, særlig samtaler med noen i utlandet. Det har ført til at mange etiopiere i utlandet er redde for å ringe hjem til Etiopia.
En tilhenger av opposisjonen fortalte Human Rights Watch at en dag han ble pågrepet, viste politiet en liste over alle oppringninger han hadde fått og gjort og spilte av en samtale han hadde med broren.
- De pågrep meg fordi vi snakket om politikk på telefonen. Det var den første telefonen jeg hadde hatt, og jeg trodde jeg kunne snakke fritt.
Selv om det er forbeholdt de relativt rike å ha mobiltelefon, og iallfall internett, øker dekningen kraftig. Det utnytter regimet til å utøve sensur, eller indirekte ved at brukerne sensurerer seg selv.
Organisasjonen har også snakket med eiere av internettkafeer. En av dem fortalte HRW at myndighetene hadde krevd at alle dataskjermene måtte være synlige slik at de ansatte på internettkafeen kunne rapportere «uvanlig oppførsel».
En annen kaféeier fortalte at hun ble truet med fem år i fengsel fordi noen av gjestene hadde vært inne på sider med kritisk innhold mot myndighetene.

Human Rights Watch says Ethiopia is using some of the world's most advanced surveillance software to monitor communications from Ethiopians at home and abroad

Human Rights Watch says that the Ethiopian government is spying on its citizens and monitoring the activities of Ethiopians in the diaspora by using high tech software from China, Italy and Germany.
Felix Horne s the Horn of Africa researcher with the international human rights organization. He says the Ethiopian government has unlimited access to records of phone calls and emails of Ethiopians at home and abroad:
“Inside Ethiopia, its control of its Chinese developed telecom system results in having unfettered access to phone records and metadata of all phone calls in the country," he said. "Outside the country, they are using western-made technology to target the activities of very specific members of the diaspora. These technologies are being provided by a company in Italy, called HackingTeam and a company in Germany called Gamma.”
Ethiopia’s telecommunication is monopolized by the state-owned Ethio Telecom. A sim card can only be obtained in Ethiopia after registering personal details, making it easy for the government to identify domestic callers, according to Human Rights Watch.
A U.S. citizen of Ethiopian origin filed a lawsuit against the Ethiopian government last month, saying his computer had been hacked and he had been spied on for more than four months.
Horne says that certain ethnic groups feel particularly at risk when answering phone calls from abroad.
He says, “One of the things that we found in our research is that individuals that receive phone calls from abroad are often targeted and accused of talking to banned organizations or of plotting something against the government, despite there being little evidence to that effect.”
Redda, an adviser to Ethiopia's prime minister, denies the Human Rights Watch report. He says the group has "made it a habit to accuse Ethiopia of almost everything that goes wrong in the region" and it has a "negative knee-jerk reaction about any developments in the country."
He adds that the government "would not waste resources in eavesdropping conversations of opposition figures" and that the accusations are "pure hogwash".

Tuesday, March 25, 2014

weyanee Regime Detained Opposition Party Leader

Mr. Getnet’s luggage was removed from the plane and he had to endure three hours of intense questioning by some TPLF so-called “security agents” which caused him to miss his flight. Mr. Getnet, educated as a civil engineer, returned to his home around 2 a.m. Saturday morning.
The TPLF government insists that it is a democratic nation concerned with only the best interests of the Ethiopian people. Yet the current regime has no qualms about denying a basic human right – the liberty for a citizen to freely move about and travel to any country he or she desires. Perhaps America is secretly forbidden to young Ethiopian leaders by the ruling government, fearful that these young people may learn too much about democracy and a free citizenry.
YALI was initiated by American President Barack Obama in 2010. He wanted a program, set up through the U.S. State Department, to strengthen young African leaders as they “spur growth and prosperity, strengthen democratic governance, and enhance peace and security across Africa.” Because of the TPLF actions that stopped Mr. Getnet’s travel, these high goals must be troublesome to the corrupt ruling regime.
The ruling powers in Ethiopia can still claim the U.S. as an ally. But, the present regime should be wary about preventing a young Ethiopian from visiting American shores to learn about economic growth, commercial prosperity, and human rights. President Obama set up thisprogram himself. Surely he and his state department, along with American citizens in general, will finally see the farce in this alliance with a dictatorial regime that tramples the rights of its citizens. As of yet, no comment has come from either President Obama or the U.S. State Department regarding Mr. Getnet’s detention.
This is not the first incident in 2014 that marks the repression and terror the current regime has visited on Semayawi Party members and their supporters. In early February, 14 were arrested in the city of  Gondar as they planned a peaceful demonstration to take place in the city’s Mesqel Square. Four executive leaders were among them: Getaneh Balcha (Organization Affairs), Yidenkachew Kebede (Legal Affairs), Berhanu Tekeleyared (Public Relations), Yonatan Tesefaye (Youth Affairs). Two drivers and a camera man were also arrested. Cameras and laptop computers were confiscated.
More recently, Semayawi Party members were arrested and some badly beaten during a protest at a 5k Women’s Great Run event. The women runners used the event to protest the strangle-hold the ruling regime has on the liberties of the Ethiopian people. As is standard with terrorist organizations, the regime’s goons took the women away in the night for interrogation and threatened them with guns held to their heads.
Other parties in opposition to the current regime’s tyranny exist, such as the Andinet and the All Ethiopian Unity Party (AEUP). The Semayawi Party is distinguished by its youthfulness. Most members are under the age of 35 and seem somewhat fearless in the face of state police brutality and the regime’s terrorizing of its own citizens.
The Semayawi Party, also known as the Blue Party, became part of the opposition front during June of last year when a huge rally formed in Addis Ababa. Demonstrators were protesting the unlawful jailing of journalists, and religious and political leaders..
When a regime bans or restricts social media and confiscated cell phones, that is evidence that the regime is restricting or banning the rights of its populace to free speech and other civil expression.
Among other crimes, the current regime is evicting people from their heritage lands and leasing thousands of acres to foreign  corporations – regime cronies pocket the monetary reward. Corruption and poverty presently are endemic in this ancient land and the populace at large deeply resents the ruling regime. The Semayawi Party hopes to forge a unity with other opposition parties, and the Ethiopian populace, to bring about the necessary political change that will allow a truly democratic government to prevail and serve the Ethiopian people.
Last summer, Mr. Getnet vowed that if social and economic issues such as unemployment and inflation were not dealt with soon, that his party would organize more protests. “It is thebeginning of our struggle,” he said.

Monday, March 24, 2014

ሕወሓት ሰራሾች እና ሕዝቡ ከንፈር ተነካክሰዋል።

ሸዋ በር እና አከባቢው ስጋት ነጋደው ጭንቀት እንዳጠላበት ነው።"...አዘናግቶ ሊያጋየን ነው::"
የእሳት ማጥፊያ አዘጋጁ እሳት ሊነሳ ይችላል የሚለውን ወያኔያዊ ሽብር በነጋዴዎች ዘንድ ጥርጣሬ አጭሯል::

በሃረር ለረዥም ጊዜ ታፍኖ የቆየው ብሶት ባለፈው ሰሞን የተነሳውን የእሳት ቃጠሎ ተከትሎ ሕዝቡ አደባባይ እስከመውጣት ደርሶ ነበር::የወያኔው መንግስት ካለፉት አመታቶች ጀምሮ በተለያየ ጊዜ የሃረር ነጋዴዎችን መደብሮች ሲያቃጥል እንደ ዋናው ምክንያት ተደርጎ የተወሰደው አከባቢው ለልማት ስለሚፈለግ ከቦታው ተነሱ የሚለው የቅድመ ማስጠንቀቂያ ነጋዴዎቹ በምትኩ ቦታ ይሰጠን የሚሉትን አስታኮ የሚመጣ ቃጠሎ መሆኑ እና ከቃጠሎ በፊት ወደ መደብሮች መጋዘን የሚገቡ ነዳጅ የተሞሉ ጀሪካኖች ሕዝቡ ጣቶቹን በወያኔ ላይ እንዲጠቁም አድርጎታል::
ወያኔ የሃረር ህዝብ ላይ ያደረሰውን ሰቆቃ እና በደል ለመሸፈን ሰላማዊ ሰልፍ በመጥራት ነገሮችን በሙሉ አሸባሪ ብሎ በሚጠራቸው በመላከክ ህዝቡን ለመሸወድ ቢሞክርም አልተሳካለትም:: በየመንገዱ ቢያፍስ ቢያባርር ቢደበድብ ቢያስር ስብሰባ ቢጠራ ያልተሳካለት ወያኔ ከዚህ በመቀጠል ምን ሊያመጣ እንደሚችል እስካሁን የታወቀ ነገር የለም:: ምናልባት ይላሉ የሸዋ በር እና አከባቢው ነጋዴዎች ስጋታችንን እና ጭንቀታችን መደብሮቻችንን እንዳያቃጥልብን ነው ሲሉ ሃሳባቸውን አካፍለውናል::
በውሃ እጥረት እና በሌሎች የአገልግሎት አቅርቦት የምትታመሰው ሃረር በሕወሓት ሰራሾች ደባ እየተደረገባት ያለው የሰብኣዊ መብት ገፈፋ እና በደል እየጨመረ እንዲ እየቀነሰ አለመሆኑ የሰሞኑ ምስክር ሂደት ምስክር ነው::በዚህ ሰሞን ከክልሉ ምክር ቤት እስከ ቀበሌ ካድሬዎች ስብሰባ ከሕዝቡ እስከ ነጋዴው ቢሰበሰብም በሰብሳቢዎች እና በተሰብሳቢው ሕዝብ መካከል አለመተማመን እንደነገሰ ተበትኗል:: በትላንትናው እለት በሸዋ በር አከባቢ ጀጎል ግንቡን አስታኮ ያሉ ባለመደብሮች ስብሰባ ተጠርተው እንዲሁም የእህል እና የቅመማ ቅመም ነጋዴዎች በስብሰባው ተጋብዘው የተገኙ እና በተሰብሳቢው እና በሰብሳቢዎች ሕወሓት ሰራሽ የከተማው ባለስልታናት መካከል ስጋት እና ሽንቀት ወጥሮት የተካሄደ እንደነበር ነጋዴዎቹ ጠቁመዋል::
የሸዋ በር አከባቢ ነጋዴዎች ባለፈው በመብራት ሃይል እና በሲጃራ ተራ አከባቢ የደረሰውን የእሳት ቃጠሎ ከተመለከቱ በኋላ ነግ በኔን በማሰብ ንብረታቸውን ከአከባቢው በማሸሽ ስጋታቸውን በተግባር ለወያኔ ሰራሽ አካላቱ ያሳዩ ሲሆን ይህንን የተመለከተው መንግስታዊ አካል ነኝ ያለ ክፍል ነጋዴው እቃውን ከማውጣት ከመንግስት ጋር በጠረጰዛ ዙሪያ እንሰብሰብ እቃችሁን አታሽሹ ቢልም ነጋዴዎቹ አዘናግቶ ሊያጋየን ነው በሚል እቃቸውን ወደቤታቸው ጭነው ወስደዋል::
ንብረታችን ቤታችን እንዳለ ስብሰባ እንቀመጣለን ብለው የቆረጡት ነጋዴዎች በተጠሩበት ስብሰባ በመሄድ ዋና ዋና የተባሉ ነጥቦችን አንስተዋል::ከተነሱት ነጥቦች በእሁድ ቀን ማንም ሰው በገበያ ቦታዎች ውስጥ መገኘት እንደማይኖርበት;እሁድ ቀን ጠቅላላ መደብሮች ዝግ መሆን እንዳለባቸው:የዘበኞች ቁጥር መጨመር እንዳለበት:ወዛደሮች መታወቂያ እና ባጅ ሊኖረው እንደሚገባ እና መቆጣጠር አስፈላጊ መሆኑን:በንግዱ አከባቢ ዳር ዳሩን የመኪና መንገድ ላይ ያሉ በረንዳዎች እና መደቦች መጽዳት እንዳለበት በገበያ ውስጥ እሳት ማጥፊያዎች እና የውሃ ታንከሮች እንዲዘጋጁ ተወያይተውባቸዋል:; በዚህም መሰረት ነጋዴዎቹ የመተማመን መንፈስ ባይታይባቸውም ወኪሎቻቸውን መርጠው ስራውን ሊሰሩ የተስማሙ ሲሆን እስከዛሬ ያልታሰበ የእሳት ማጥፊያ እና የውሃ ታንከር አዘጋጁ እሳት ሊነሳ ይችላል የሚለውን ወያኔያዊ ሽብር በጥርጣሬ ተመልክተውታል::
ይህ በእንዲህ እንዳለ ከታች በአስተያየት መስጫ ውስጥ የምትመለከቱት ምስል ከሶስት አመት በፊት ቦታው ለኢንቨስትመት ይፈለጋል ተነሱ የተባሉ ነጋዴዎች ምትክ ቦታ ይሰጠን እያሉ ሲከራከሩ የወያነ ሰራሽ የክልሉ ባለስልጣናት በድንገት የነጋዴዎችን መደብሮች ያቃተሉት ቦታ ሲሆን ይህ ቦታ ወደ መብራት ሃይል ሂደው ባለፈው ሱቆቻቸው የተቃተሉባቸው ነጋዴዎች ቦታ የነበረ ነው:: መንግስታዊ እሳት እየተከተለን ነው የሚሉ የመብራት ሃይል መደብር ባለቤቶች እና ተጎጂዎች ከ3 አመት በፊት የተቃጠለባቸው ቦታ ሕንጻ ለማሰራት ለአንድ ኢንቨስተር ተሰቶት ጥናት ተካሂዶ ቦታው ለኮንስትራክሽን አመቺ እንዳልሆነ እና አከባቢው ውሃ የሞላበት እና ሕንሳ ሊያሰራ የማይችል አፈሩም ለሕንሳ ግንባታ ተስማሚ እንዳልሆነ ይህ ቦታ ላይ ህንጻ ለማስገንባት ከፍተኛ ወጪ እና ዲዛይን የሚጠይቅ በመሆኑ ቦታው በዚህ ምክንያታዊ ጉዳዮች ለ3 አመት ያህል በምስሉ እንደምታዮት ታጥሮ የነበረ ሲሆን በአሁን ሰአት የተቃጠለው የሲጃራ ተራ እና የመብራት ሃይል ከቃጠሎ የተረፉ ቆርቆሮዎች እና ሌሎች ማቴሪያሎች መከመሪያ እየሆነ ነው::

Friday, March 21, 2014

በኦሮሚያ ቡሌ ሆራ ዩንቨርስቲ ራሳቸውን የሚያጠፉ ተማሪዎች ቁጥር እየጨመረ ነው::

ትላንት ለሊቱን አንዲት የፕላንቴሽን ሳይንስ ተማሪ ሞታ ተገኝታለች
በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን በጉጂ ኦሮሚያ ቡሌሆራ ከተማ በሚገኘው እና ቡሌ ሆራ ተብሎ በሚጠራው ዩንቨርስቲ ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች በሚደርስባቸው የአስተዳደር በደል እና በመማር ማስተማሩ ላይ በሚደረጉት ፖለቲካዊ ተጽእኖዎች
ራሳቸውን የሚያጠፉ ተማሪዎች እና ትምህርታቸውን ጥለው የሚወጡ ተማሪዎች መበራከታቸውን ከዩንቨርስቲው የደረሱን እገባዎች ያመለክታሉ::
በዩንቨርስቲው ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች በአሁን ጊዜ ወደ 3000 የሚጠጋ መሆኑን የነገሩን ምንጮች ከእለት ወደ ኢለት በብሶት የተማረሩ ተማሪዎች ራሳቸውን ማጥፋት የቀጠሉ ሲሆን በዚህ አመት ብቻ የአሬውን ጨምሮ አራት ተማሪዎች ራሳቸውን አጥፍተዋል:: እንዲሁም አንድ ተማሪ ከፎቅ ላይ ዘሎ በመውደቅ ራሱን ለማጥፋት ቢሞክርም ተርፏል::
ቁጥራቸው ከ500 በላይ የሆኑ ተማሪዎች በተለያየ ዩንቨርስቲው በሚፈጥረው የአስተዳደር እና የፖለቲካ ጉዳዩች ብስጭት ራሳቸውን በመሳት ወደ ቤተሰቦቻቸው ትምህርታቸውን አቅውርጠው ተመልሰዋል::በዛሬው እለት ደግሞ የፕላንቴሽን ሳይንስ የሁለተኛ አመት ተማሪ የሆነች ለሊቱን ሞታ መገኘቷን ታውቋል::

Thursday, March 20, 2014

በሃይል ግንባታ ሰበብ በህዝብ ላይ መንግስታዊ አሻጥር እየተፈፀመ ነው::

አቤቱታችን ከፖለቲካ ነጻነት እና ዲሞክራሲያዊነት ጎን ለጎን የመሰረታዊ አገልግሎቶች ጥያቄ ነው ...ይህ ደሞ ለየት ባለ መልኩ አብዮታዊ ነው::እኛ በሰው አገር የምንኖር ዲያስፖራዎች በወገናችን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ከማውራት እና መኖሪያ ፍቃዳችን ሲታደስ ከመቀዝቀዝ ዉጪ በወያኔ ላይ የምናሳድረው ጫና እምብዛም ጉልፍ ስፍራ የለውም:: እርስ በርሳቸው የሚላተሙ የጆተኒ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች በላም አለኝ ተስፋ ህዝባችንን አረንቋ ውስጥ እየጨመሩት ነው::
ለጋች አገራት የሚያወጧቸው ሃሰተኛ ጸረ አፍሪካ ሪፖርቶች በተለይ የምስራቅ አፍሪካን ተገን አድርጎ የተመቻቸው የብሄራዊ ጥቅማቸው ፎርሙላ ስኬት የአምባገነኖችን እድሜ በማስረዘም ህዝብ እንዲጭበረበር የህዝብ ጥያቄዎች እንዲደናቀፉ ለገዢዎቻችን የልብ ልብ ሰቷቸዋል:: ለብሄራዊ ጥቅም አስጊ ይሆናሉ የተባሉ የፖለቲካ ድርጅቶችን እስከማጨማደድ እየዘለቀ በኢጅ አዙህ ህዝባዊ ጥያቄዎች እንዲታፈኑ እየተደረገ አምባገነናዊ አገዛዝን አፍልተውብናል እንሱ ለጋሽ አገራት::
መሰረታዊ ፍላጎቶች እና የአገልግሎት ፍጆታችን በበቂ ሁኔታ ባልተሟላበት አገር መንግስት ፕሮጀክት ለመጨረስ የገንዘብ እጥረት ገጠመኝ በሚልበት አገር ብሄራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሬ የለኝም በሚልበት እና የመንግስት ካዝና ባዶ ሆኖ በዕቃ ግምጃ ቤት ሰነድ ጨረታ ከቱጃሮች መንግስት በሚበደርባት አገር ጥቂት ፖለቲካው የወለዳቸው ሃብታሞች እጅግ ብዙ የኢኮኖሚ ድቀት ያፈራቸው ደሃዎች በፈሉበት አገር ምን አይነት የኢኮኖሚ እድገት እንደተመዘገበ አነጋጋሪ ነው:; እስከመቼ የአምባገነኖችን ደጋፊዎች ዉሸት ተሸክመን እንዘልቃለን::
መብራት ውሃ ስልክ ሀገሪቷ ተሰርቶ እና ተበድራ ሳይሆን በተፈጥሮ የታደለችው ጸጋዋ እንደሆነም ያለን ሃብት ይመሰክራል ህዝቡ ያለውን ቴክኖሎጂ ከተፈጥሮ ሃብቱ ጋር አደባልቆ እንዳይጠቀም እኛ እናውቅላቹዋለን የሚሉ የወያኔ አውሬዎች ቀፍድደው ይዘውታል::
በቀላል ሊፈታ የሚችል ችግርን በፖለቲካዋ ሳንካ መተብተብ ምንም የሚጠቅም ስላልሆነ ህዝቡ አስፈላጊውን የአገልግሎቶች አቅርቦት እንዲያገኝ መደረግ አለበት ብለን ካሁን በፊት ብንጮህም ከቀድሞ በባሰ መልኩ ብሶበት ይገኛል::
በአለማችን በረሃ በተባሉት አገሮች የውሃ አቅርቦት በሰፊው ለህዝባቸው እየሰጡ ሲሆን የተጣሩ ውሃዎች ሳይቀር በርካሽ ዋጋ እየተሸጡ ነው::በኢትዮጵያችን ግን በተፈጥሮ የታደልነውን ውሃ በፖለቲካ ሹማምንት ልፍስፍስነት ልንጠቀምበት አልቻልንም ትልልቅ እና ገባር እንዲሁም ትንንሽ ወንዞች እና የተፈጥሮ ውሃ ምንጮች በሞሉባት ሃገራችን ህዝብ ውሃ ተጠማሁ ሲል መመልከት አስደንጋጭ ነው::ሃገሪቱ በውሃ ችግር ተውጣልች::የውሃ እጥረት ኖሮን ሳይሆን በአግባቡ አለመጠቀም እና ችግሩን የመፍታት ባህል ስላሌለን ነው::ለጎረቤት አገሮች ውሃ እንሰጣለን እየተባለ ባለበት የፕሮፓጋንዳ ጡዘት ውስጥ እኛ በጥማት ማለቃችን አሳፋሪ ነው::
ወድ መብራት ስንመጣ ደሞ መንግስት ያለ እንኳን ተደርጎ ማሰብ ይከብዳል:: የኢትዮጵያ ዲሞክራሲ መብራት ጠፍቶ ሲመጣ መብራት መጣ ብሎ መጮህ ነው ተብሎ በሰው ሃገር ጋዜጦች እስኪቀለድብን ድረስ ወያኔ በህዝብ ጭንቅላት ጢባጢቦ እየተጫወተች ነው::ይህ እንደገጠመኝ እና እድል የሚታየው የመብራት እቃቃ ጨዋታ በአግባቡ መፍታት እየተቻለ ችግሩንም ማድረቅ እየተቻለ ለምን መዘናጋት እንደሚፈጠር ማስረዳት የሚችል ባለስልጣን አልተገኘም::በኤሌክትሪክ መጥፋትና ሥርዓት አልበኝነት ምክንያት በርካታ ኢንዱስትሪዎች ሥራቸውን እያቆሙ ናቸው፡፡ በርካታ ማሽኖች ከጥቅም ውጭ እየሆኑ ናቸው፡፡ በመኖሪያ ቤቶች ቴሌቪዥኖች፣ ፍሪጆችና ሌሎች የኤሌክትሪክ ዕቃዎች እየፈነዱና እየተቃጠሉ ነው፡፡ በመብራት መጥፋት ምክንያትም የየዕለቱ ኑሮ ይዘቱም ገጽታውም እየተበላሸ ነው፡፡ ከመኖሪያ ቤቶች አልፎ ካፌዎችም በመብራት መጥፋት ምክንያት ‹‹ተረኛ መድኃኒት ቤት›› እየመሰሉ ነው፡፡ ሻይ ታዞ ‹‹ይቅርታ መብራት የለም›› የሚል መልስ መስማት የተለመደ እየሆነ ነው፡፡ እውነት ኢትዮጵያ ለዜጎቿ፣ ለኢንዱስትሪዎቿም ሆነ ለሁሉም ዓይነት እንቅስቃሴዎቿ የሚሆን በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል የላትም? አይኖራትም? አላትም ይኖራታልም፡፡ በቂ የውኃ ኃይል ማመንጫዎች የንፋስ የኃይል ማመንጫዎች የፀሐይ የኃይል ማመንጫ አቅም የጂኦ ተርማል የኃይል ማመንጫ አቅምም አለ፡፡ እንኳን ለራስዋ ለሌሎች አገሮችም የሚሆን የኤሌክትሪክ አቅርቦት ዕምቅ ሀብት አላት፡፡ ኦኖም ግን በአግባቡ የሚያዳርስ እና የመልካም አስተዳደር ችግሮች አጣብቂኝ ውስጥ ስለከተቷት ህዝቧ አስፈላጊውን የአገልግሎት መብቶች እና አቅርቦቶች ሊያገኝ አልቻለም::በሃይል ግንባታ ሰበብ በህዝብ ላይ መንግስታዊ አሻጥር እየተፈፀመ ነው::
ወደ ስልክ እና ኢንተርኔት ኔትወርክ ስንመጣ በጸሎች የሚገኝ ያውም ተለቅሶ መፍትሄም የጠፋለት ጉዳይ ከሆነ ቆይቷል:: በአለማችን በስፋት ይህን የኔትዎርክ ችግር ተቀርፎ ባለበት ሰአት የወያኔ ባለስልጣናት ግን በአደናባሪዎቻቸው በኩል በፋይበር ቅንጠሳ እና በህንጻ መብዛት ቢያሳስቡም ከነሱ ቀድሞ ንቃተ ህሊናው ያደገውን ህዝብ ግን ሊሸውዱት አልቻሉም:: ያው እንደለመዱት በጠበንጃ እና ሽብር በመንዛት ዝም አሰኝተውታል:: የወያኔ መንግስት የህዝብን የአገልግሎት አቅርቦት ጥያቄዎች መፍታት እየቻለ እንዳይፈቱ በማድረግ በሚፈጸም አሻጥር እራሱ አጣብቂኝ ውስጥ እንደገባ ሊገነዘበው አልደፈረም:: የመልካም አስተዳደር ብልሃት የሞላበት አመራር ህግ አክባሪ እና አስከባሪ ባለስልጣንትን ለማግኘት ሁላችንም በትግሉ ላይ እንረባረብ !!!

በኩዌይት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ናቸው

ውጥረቱ የተጀመረው አንዲት ኢትዮጵያዊት አንድ የአገሪቱን ባለስልጣን ልጅ መግደሉዋን ተከትሎ ነው። ኢትዮጵያዊቷ ግድያውን የፈጸመችበትን ትክክለኛ ምክንያት ለማወቅ ባይቻልም፣ ገዳዩዋን በቅርብ እናውቃለን ከሚሉ ወገኖች የተገኘው መረጃ በቂም በቀል ተብሎ የተደረገ መሆኑን ኢትዮጵያውያን ይገልጻሉ። ከሶስት አመት በፊት ወደ ኩዌት የገባችው ወጣት በመጀመሪያው ወር በአሰሪዋ ልጅ መደፈሩዋን ለመበቀል በሚል የባለስልጣኑን ልጅ ለመግደል እንደተነሳሳች መግለጿን ኢትዮጵያውያን ይናገራሉ።
የኩዌት መንግስት ስለ ግድያው መንስኤ እስካሁን በኦፌሴል ያሳወቀው ነገር የለም። ይሁን እንጅ የኩዌት የፓርላማ አባላትና አንዳንድ ባለስልጣናት ኢትዮጵያውያን ከአገራቸው እንዲወጡ እየወተወቱ ነው።
የሟች አክስት የሆነች አንዲት ማንነቱዋ ያልተገለጸ አሰሪ ከአራት ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞች መካከል እጣ በማውጣት አንደኛዋን ኢትዮጵያዊት በማረድ የአክስቷን ልጅ ሞት መበቀሉዋን ኢትዮጵያውያን በፎቶ ግራፍ አስደግፈው ለኢሳት የላኩት መረጃ ያሳያል።
ኢሳት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን ከቤት ለመውጣት እንዳልቻሉ፣ ከቤት ቢወጡ ተይዘው እንደሚታሰሩ ወይም የበቀል ሰለባ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት በፍጥነት ደርሶ አሁን የተፈጠረውን ውጥረት እንዲያረግብም ኢትዮጵያውያን ተማጽነዋል። በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁኔታውን በንቃት እንዲከታተሉት ጥሪ አቅርበዋል። ኢሳት የኩዌት ባለስልጣናትን ለማነጋገር ያደረገው ሙከራ አልተሰካም።

Tuesday, March 18, 2014

የኦህዴድ አባላት በአቶ አለማየሁ ሞት ጉዳይ ጥያቄ እያቀረቡ ነው

የኦሮሚያ ክልል እና የኦህዴድ ፕሬዚዳንት የነበሩትና ሰሞኑን ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የአቶ አለማየሁ አቶምሳ የሞት መንስኤ እንዲጣራ የኦህዴድ መካከለኛና ዝቅተኛ ካድሬዎችና አባላት በየመድረኩ ጥያቄ እያነሱ መሆኑ ከፍተኛ አመራሩን ጭንቀት ውስጥ እንደጣለው ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለጹ፡፡
አቶ አለማየሁ ለሞታቸው መንስኤ የሆነው ከምግብ ጋር የተሰጣቸው መርዝ ነው የሚሉ መረጃዎች ኢሳትን ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ይፋ መሆኑን ተከትሎ አብዛኛዎቹ መካከለኛና ዝቅተኛ የድርጅቱ አባላትና ካድሬዎች የአቶ አለማየሁ ሞት በገለልተኛ ወገን ተጣርቶ እንዲቀርብ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ጥያቄ ማቅረብ ጀምረዋል፡፡
በተለይ ከአቶ አለማየሁ ሞት ጀርባ የቀድሞ የኦሮሚያ ፕሬዚደንት አቶ አባዱላ ገመዳ እጅ አለበት መባሉና ጉዳዩም ሙስናና ኪራይ ሰብሳቢነትን ጠራርጎ ለማጽዳት አቶ አለማየሁ የጀመሩት እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ ሆን ተብሎ የተፈጸመ ነው በሚል መገለጹ አብዛኛውን የድርጅቱን አባላት ቁጭት ውስጥ ጥሏል፡፡
በዚህም ምክንያት አቶ አለማየሁ የጀመሩትን የኪራይ ሰብሳቢነትና የሙስና ትግል አጠናክረን እንቀጥላለን የሚሉ መፈክሮች በየወረዳውና በየቀበሌው በስፋት በመስተጋባት ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡
አንድ ለጉዳዩ ቅርበት ላቸው የኦህዴድ አባል ለዘጋቢያችን እንደገለጹት የአቶ አለማየሁ ሞት እንዲጣራ ጣያቄ ሲቀርብ ከፍተኛ አመራሩ ይሄ የጸረ ሰላም ሃይሎች አሉባልታ ነው በሚል ምላሽ ለመስጠትና ለማጣጣል ሙከራ እንደሚያደርጉ አስታውሰው የሁሉን አመኔታ ለማግኘት ግን ፍረጃ ውስጥ ከመግባት ይልቅ ነገሩን በገለልተኛ ወገን ማጣራቱ ይቀል ነበር በማለት ነቀፌታውን አጣጥለውታል፡፡
አብዛኛው አባላት የአቶ አለማየሁ ሞት መንስኤ እንዲጣራ እየወተወተ መሆኑንና የዚህ ጥያቄ መመለስና አለመመለስ በድርጅቱ ቀጣይ ህልውና ላይ የራሱ የሆነ አዎንታዊም ሆነ አሉታዎ ሚና እንደሚኖረው አመልክተዋል፡፡
ይህ የኦህዴድ አባላትና ካድሬዎች ጥያቄ በተለይም የኦህዴድ ስራ አስፈጻሚ ኮምቴ አባላትን አስጨንቋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በቅርቡ የሰልጣን ሽግሽግና አዲስ ሹመት ያገኙትን ጨምሮ ኦህዴድን በመምራት ላይ የሚገኙት ስራ አስፈጻሚዎች አቶ ሙክታር ከድር ሊቀመንበር፣ወ/ሮ አስቴር ማሞ ምክትል ሊቀመንበር፣አቶ ዘላለም ጀማነህ፣አቶ ግርማ ብሩ፣አቶ አባዱላ ገመዳ፣አቶ ኩማ ደመቅሳ፣አቶ ሶፊያን አህመድ፣አቶ ድሪባ ኩማ፣አቶ አብዱልአዚዝ አህመድ አባላት መሆናቸው ይታወቃል፡፡

Monday, March 17, 2014

በዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን ዝክር፤ በእህቶቻችን ኮርተናል!

ለዘንድሮው ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን መታሰቢያ በአዲስ አበባ ከተማ በተደረገው የሩጫ ትዕይንት ላይ ወጣት ሴቶች ባሳዩት ልበ ሙሉነት ኮርተናል። የሩጫውን ትዕይንት አስታከው፣ በአብዛኛው የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እንደሆኑ የተነገረላቸው ወጣት ሴቶች ለፍትህ፣ ለነፃነት፣ ለህሊና እስረኞች መፈታት እና ለሀገር አንድነት ድምፃቸውን ከፍ
አድረገው ጮኸዋል፤ ዘምረዋል። እነዚህ ወጣት ሴቶች በሥርዓቱ ምን ያህል እንደተማረሩ በቃላትም በአካል ንቅናቄም አሳይተዋል። ዘረኛውና ፋሽስቱ ወያኔ ግን “ለምን ተቃወማችሁኝ” ብሎ አስሯቸዋል፤ ከፊሎቹም የደረሱበት አይታወቅም። በእህቶቻችን ቆራጥነት ኮርተናል፤ በወያኔ የፈሪ ዱላ ደግሞ ተቆጥተናል። በ1997 እና 98 “የወላጆቻችን ድምጽ ይከበር” ያሉ ሕፃናትን የጨፈጨፈው ወያኔ በ2006 ወጣት ሴቶችን ከማሰቃየት ይመለሳል ብለን አናምንም። ወያኔ እስካልተወገደ ድረስ የፈሪ ዱላው የማይቀር ነገር ነው።
የወንዶቹን ያህል የተዘገበ አይሁን እንጂ በክፉም በደጉም ሴቶች ያልተሳተፉበት የኢትዮጵያ ታሪክ የለም። የቅርብ ጊዜ ታሪካችንን እንኳን ብናይ በፋሽስት ወረራ ወቅት ኢትዮጵያዊያን ሴቶች በአርበኝነት ዘምተው አዋግተዋል፤ ተዋግተዋል። በተለያዩ ምክንያቶች መዝመት ያልቻሉት ደግሞ በውስጥ አርበኝነት ተሰልፈው የጠላት ምስጢሮች ለአርበኞች እንዲደርሱ በማድረግ ከፍተኛ ጀብዱዎችን ፈጽመዋል። ከፋሺስት ወረራ ወዲህ በነበሩ ዓመታት ውስጥም ለፍትህ እና ለነፃነት በተደረጉ ተጋድሎዎች ሴቶች ጉልህ ተሳትፎ ነበራቸው።

Sunday, March 16, 2014

በሕወሓት ጄኔራሎች እና በብኣዴን የጦር መኮንኖች መካከል ውጥረት ነግሷል

ጄኔራል አበባውን ወደ ሲቭል ባለስልጣንነት የመቀየር እቅድ ተይዟል
ህገመንግስታዊ ጥያቄ ባነሱ ከጄኔራልነት እስከ ሻምበልነት ማእረግ ባላቸው የቀድሞው የኢሕዴን ታጋዮች እና የአሁን የብኣዴን የጦር መኮንኖች እና በሕወሃት ጄኔራሎች መካከል ከፍተኛ የሆነ የመብት ጥያቄዎችን ያማከለ እና ህገመንግስታዊ ስርኣትን ተከትሏል የተባለለት ጥያቄዎችን ተከትሎ ከፍተኛ ውጥረት መከሰቱን የመከላከያ ምንጮቻችን ጠቁመዋል::

ባለፉት ሰሞናት የተደረጉት ስብሰባዎች በከፍተኛ አለመግባባት የተበተኑ ሲሆን በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ በስፋት የፓርቲ ስራዎች እንጂ ሃገራዊ ስራዎች እየተሰሩ አይደለም የሚሉ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊቱ ለህገመንግስቱ መከበር ተገኢ መሆን አለበት በአሁን ወቅት ለአንድ የፓርቲ አመራር እና ለፕሮፓጋንዳ ተገኢ ሆነናል የሚሉ ተመሳሳይ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በሰራዊቱ ውስጥ ያለውን የእድገት የትምህርት እና የደምወዝ መብትን በተመለከተም ከፍተኛ ክርከር ቢደረግም ካለመግባባት መኮንኖቹ ጥርስ እንደተነካከሱ ወደየመጡበት ተበታትነዋል::

የሰራዊት አባላትን ለመቀነስ በተደረገው ጥናት መሰረት ለምን ሁለት ብሄር ላይ አተኮረ የሚሉ ጥያቄ እንዲሁም የስኮላርሺፕ አድሏዊነት በተመለከተ ጠንከር ያሉ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን እንዲሁም ከአንድ ብሄር ለትምህርት ተመርጠው የሚላኩ መኮንኖች በዛው ሳይመለሱ ይቀሩና ነገሩ ይድበሰበሳል የሚሉ አስጨናቂ ጥያቄዎች ተከታትለው ቢነሱም ከመድረኩ መልስ ሳይሰጥባቸው ተድበስብሰው አልፈዋል::ከአንድ ብሄር ብቻ ተመርጠው ለትምሕርት አውሮፓና አሜሪካ ከሄዱት መኮንኖች 80 ከመቶ ያልተመለሱ ሲሆን ይህ ጉዳይ ተድበስብሶ ሌላው ብሄር ስኮላሺፕ እንዳያገኝ ምክንያት እየተፈጠር በዚያው ስለምትከዱ ሃገር ውስጥ በቂ አካዳሚ ስላለ እዚህ እንድንማር ይደረጋል::ስኮላሺፕ የሚሰጣቸው ለማይመለሱ መኮንኖች ነው የሚሉ አቤቱታዎች ተሰምተዋል::

በሕወሓት ጄኔራሎች እና በብኣዴን ከፍተኛ የጦር መኮንኖች መካከል የተነሳውን ፍጥጫ ተከትሎ ጄኔራል አበባውን ወደ ሲችል ባለስልጣንነት ለማዘዋወር የታቀደ መሆኑን የገለጹት ምንጮሽች በአሁን ሰአት ጄኔራሉ እንደ ቁም እስረኛ አብዛኛው ጊዜያቸውን በመኖሪያ ቤታቸው እንደሚያሳልፉ እና ወደ ቢሯቸው አልፎ አልፎ እንደሚገቡ ታውቋል::


የሳሞራ የኑስን ስልጣን ይረከባሉ ተብሎ የሚጠበቀው ጄኔራል አበባው ጄኔራል ዮሃንስን ወደ ሳሞራ ሕወሓት በሹመት አቅርቦ ካመጣቸው በኋላ ይተለያየ ተጽእኖ እየተደረገባቸው ቢሆንም የብኣዴን ፓርቲ አመራሮች ሁኔታውን በቅርብ እየተከታተሉ ነው ቢባልም ምንም አይፈጥሩም የአሽከርነት ሚና ካልሆነ በስተቀር ሲሉ ምንጮሹ ገልጸዋል::የጄኔራል አበባው ስልጣን ማቆም እና ወደ ሲቭል ባለስልጣንነት መቀየር በሃገሪቱ የፖለቲካ ሂደት ላይ የሚያመጣው ለውጥ እንዳይኖር ሁኔታዎች እየተገመገሙ መሆኑ ታውቋል::ከዚህ ቀደም በተለያየ ወቅት ወደ ውጪ ለእረፍት ለመሄድ ጥያቄ ያቀረቡት ጄኔራል አበባው በተለያየ ምክንያት ሲሰናከልባቸው የቆየ ሲሆን እሳቸውን እና መሰላቸውን ከሰራዊቱ በዘዴ እና በብልሃት ገፍቶ ለማስወጣት በስፋት እየተሰራ መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል::ካሁን ቀደም ሜጄር ጄኔራል የነበሩት አባዱላ ገመዳ አቶ ተብለው ወደ ሲችል ባለስልጣንነት ሲዘዋወሩ ሁለት ከፍተኛ የጦር ጄኔራሎች ደግሞ ወደ እስር ቤት መወርወራቸው አይዘነጋም::

Friday, March 14, 2014

ሳይታረስ አይታጨድም። ሳይወቃ አይፈጭም

 ጥቂቶች የሚያደርጉት የፖለቲካ ዉሳኔ ዝምታ የመረጥነውን ቤታችንን አንኳኩቶ እኛን መንካቱ ፣ ማናጋቱ አይቀርም። ፖለቲካ የሚለዉ ቃል እንደ ጸያፍና አስፈሪ ቃል ነዉ በብዙ ኢትዮጵያዉያን ዘንድ የሚታየዉ። እንደዉም በተለምዶ ፖለቲካ ከኮረንቲ ጋር ይመሳሰላል። ነገር ግን፣ ይመስለናል እንጂ፣ ከፖለቲካ ነጻ የሆነ ሰዉ የለም። በአዎንታዊነት ሆነ በአሉታዊነት «ፖለቲካ አያገባንም» የሚሉ ዜጎችን ጨምሮ ፣ ምን ያህል የፖለቲካ ዉሳኔዎች፣ በእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ላይ እያደረሱ ያለዉን ተጽእኖ በስፋት ለማብራራት በርካታ ምሳሌዎችን መዘርዘር ይቻላል።

ከአራት ኪሎ የሚወሰኑት የፖለቲካ ዉሳኔዎች የማይነኩት ዜጋ አይኖርም። « ኦ ኦ ፖለቲካና ኮንረንቲ አንድ ናቸዉ. ! እኔ አያገባኝም » በሚል የፖለቲካ ፓርቲዎች ወይንም የሲቪክ ማህበራትን ተቀላቅለን ፖለቲካዊ አስተያየት ላለመስጠት ዝምታን ብንመርጥም፣ ሌሎች ጥቂቶች የሚያደርጉት የፖለቲካ ዉሳኔ፣ ወደድንም ጠላንም ቁጭ ብለን በተቀመጥንበት፣ ቤታችንን አንኳኩቶ እኛን መንካቱ ፣ ማናጋቱ አይቀርም።

ያለን አማራጭ ሶስት ነዉ።

የመጀመሪያዉ አማራጭ በፖለቲካዉ ምክንያት በቀጥታ፣ አሊያም ፖለቲካዉ በወለደዉ በኢኮኖዉ ችግር አገር ለቆ ተሰዶ መሄድ ነዉ። የቀናን ወደ አሜሪካና አዉሮፓ፣ ያልቀናን ደግሞ ወደ አረብ አገረ !!!!

ሁለተኛዉ አማራጭ ጥቂቶች በሚወስኑት የፖለቲካ ዉሳኔ ዉስጣችን እየደበነ፣ እየተቃጠለና እየተናደድን ማጉረምረምና ብሶታችንን ነጋ ጠባ ማዉራት ነዉ። ከጊዜ ወደ ጊዜ በንዴት ደም ብዛታችን እየጨመረ፣ ጸጉራችን እየሸበተ፣ ኑሮን ለመርሳት በየመሸታ ቤቱ ብርሌያችንን መጨበጥ

ሶስተኛዉ አማራጭ እጅግ ፈታኝ፣ ከራስ ጥቅም አልፎ ለሌላ ማሰብን የሚጠይቅ፣ በርግጥ ዘላቂነት ያለዉ መፍቴሄ እንዲመጣ የሚረዳ ፣ የሚያዋጣ አማራጭ ነዉ።

ዋናዉ የአገራችን ችግር የመልካም አስተዳደር፣ የእኩልነት፣ የፍትሕ እጦት፣ እንዲሁም የሙስና የዘረኝነት የጥላቻ መሳፋፋት ነዉ። በአጭሩ አባባል፣ የአገራችን ችግር የፖለቲካ ችግር ነዉ። የፖለቲካ ችግር የሚፈታዉ ደግሞ በፖለቲካ ትግል ነዉ። ይህን ተረድተን፣ የፖለቲካ ዉሳኔዎች አገርንና ሕዝብን በሚጥቀሙ መልኩ እንዲወሰኑ ለማድረግ የሰላማዊ የትጥቅ ብቻ የሆነዉን የፖለቲካ ትግል መቀላቀል የግድ አስፈላጊ ነዉ።

Wednesday, March 12, 2014

Ethiopia: Hackers Without Borders

Before Edward Snowden sparked a global debate about government surveillance, it was a fact of life for Tadesse Kersmo. During Ethiopia’s national elections, in 2005, he and his wife campaigned for the country’s pro-democracy party, the Coalition for Unity and Democracy, which achieved a sweeping victory in the capital of Addis Ababa. But, when the results were overturned and protests broke out amid allegations of fraud, the ruling party quickly began cracking down on the opposition. Observers from the European Unionreported extensive human-rights violations in the months that followed, including nearly two hundred demonstrators killed by security forces and tens of thousands more imprisoned.
Kersmo evaded arrest and moved to the countryside, but his ties to the opposition subjected him to continued threats, harassment, and intense monitoring long after the election. “It is common wisdom that the phones are tapped,” he told me, in a tired baritone, over Skype. “People would call me and tell me, ‘We are following you, we know what you’re doing, we know where you are.’ ” On three separate occasions between 2005 and 2007, Kersmo was detained and beaten. At one point, he was told that his family would find his dead body in the streets, because the prisons were filled to capacity. When that seemed imminent, in 2009, Kersmo and his wife fled to the U.K., where they were granted asylum. There he continued his work as a university lecturer and a senior member of Ginbot 7, an exiled pro-democracy party that the Ethiopian government labelled a terrorist group in 2011, under a vague and widely condemned proclamation.

Monday, March 10, 2014

Free Oromo Political Prisoners!(North Norway Oromo Youth Demonstrates in Trondheim Against the Ongoing Human Rights Violations by TPLF/EPRDF Regime)

Oromo youth in North Norway on March 1, 2014 protested against the ongoing human rights violations, inhuman killings, and the repression carried out by the criminal Ethiopian government, and the Oromo youth urged the TPLF/ERPDF to stop dictatorship with impunity.

It is unjust that the continued sufferings of the Oromo people through systematic human rights abuses by the Ethiopian government are largely ignored by governments around the world. Yet, the heinous crimes of the TPLF/EPRDF government rank high in the catalogue of human right abuses committed by African governments. Over the past two decades, the TPLF-led Ethiopian government has imprisoned tens of thousands of Oromo nationals; the situation of several thousands of innocent Oromo political prisoners has deteriorated in prisons and secret camps. Many Oromos have been (and are being) cruelly tortured, killed, uprooted, raped and exiled. Others have been abducted in broad daylight, and made to disappear or murdered secretly.

There is no peace and stability, no freedom of speech, no freedom of press, no freedom of assembly and no rule of law in Ethiopia. What truly exists is totalitarianism of one party and gross violations of democratic and human rights. The TPLF-led Ethiopian dictatorial regime’s continuation of targeting the Oromo people through brutal suppression to prolong its grab on power should not be tolerated any more.

The TPLF/EPRDF repressive “anti-terrorism” law, which came into force in 2009, has worsened the condition of Oromo individuals of all walks of life. As repeatedly reported by international human rights organizations, this law is being used by the Ethiopian government as a powerful instrument to crack down on political dissidents, including banning peaceful political demonstrations and public criticisms of government policies. Today, more than any time in the past, the Oromo people are subjected to systematic killings, disappearances, tortures, mass arrests, harassment and imprisonments in villages, workplaces, towns and cities of Oromia. The forced eviction of Oromo peasants from their ancestral farmlands through leasing several millions of hectares of Oromo lands to foreigners under obscure terms, denial of job opportunities and dismissal of employees from their jobs on flimsy excuses – are daily experiences of the Oromo people in Ethiopia.

የሃረር ከተማ በህዝባዊ ተቃውሞ እና በቶክስ እየተናወጠች ነው።

ተቃውሞው ከፖሊስ ቁጥጥር ውጪ እየሆነ ነው። የሃረር መዘጋጃ በትን ህዝቡ ከቦ በድንጋይ እያናወጠው ነው።
ምንሊክ ሳልሳዊ ትላንትና ምሽት በሃረር ከተማ በተለምዶ መብራት ሃይል በሚባል የገበያ ቦታ ላይ የወያነ ተላላኪዎች በለኮሱት እሳት ለሁለተኛ ጊዘ የነጋደውን ንብረት ማውደሙን ተከትሎ ብሶት ያረገዝው ህዝቡ አደባባይ በመውጣት ተቃውሞውን አሰምቷል።

ከሁለት አመት በፊት በዚሁ የገበያ ቦታ የወያን ተላላኪዎች በለኮሱት እሳት ከፍተኛ ንብረት መውደሙ የሚታወስ ሲሆን ትላንትና ምሽቱን በድጋሚ የእነዚሁ ተጎጂ ነጋደዎች የበፊት ቁስል ሳያገግም እና ንብረታቸውን ሰርተው ሳይተኩ በድጋሚ ቃጠሎው ተከስቷል።

የወያነው ተላላኪዎች እሳቱን እንዲለኩሱት ተደርጓል ሊባል የቻለበት ምክንያት ባለፉት ሶስት አመታት ነጋደዎቹ ከቦታው እንዲለቁ የተነገራቸው ሲሆን ከክልሉ ባላስልታናት ጋር በተነሳ አለመግባባት ባለስልጣናቱ እሳቱ እንዲለኮስ እና ንብረት እንዲወድም ያደረጉ መሆኑ ምንጮሹ ተናግረዋል።

በዛረው እለት በብሶት የተወጠረው የሃረር ህዝብ አደባባይ በመውጣት የወያነን መንግስት ያወገዘ ዚሆን ፖሊሶች ለተቃውሞ የወጣውን ህዝብ በማፈስ ወደ እስር በት የወሰዱ እና አከባቢውን በቶክስ በማናወጥ ከፍተኛ ሽብር ፈጥረዋል። እስካሁን የተጎዳ ሰው ይኑር አይኑር የወጡ መረጃዎች የሉም ።

Sunday, March 9, 2014

የኢሕአዴግ አባል ፓርቲዎች በዶ/ር ደብረጺሆን ፍቃድ ካልሆነ ምንም አይነት ውሳኔ መስጠት አይችሉም

የደህንነት ሹሙ አቶ ጌታቸው አሰፋና ባለስልጣኖቻቸው በሙስና እና በዘረፋ ላይ ተሰማርተዋል::
የፍርድ ቤቶች እና የተቃዋሚ ፓርቲዎችን እንቅስቃሴ ማኮላሸት ለአለቃ ጸጋዬ በርሄ ተሰቷቸዋል::
የጦር ሰራዊቱን በተጠንቀቅ የሚከታተሉ ወታደራዊ ደህንነቶች ተደራጅተው በየእዙ ተበትነዋል::

በመከላከያ ሰራዊት የሕወሓት መኮንኖች ስር የሰደደው የሙስና እና የዘረፋ አድራጎት በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥም ከሹሙ ከአቶ ጌታቸው እና ከባለስልጣኖቻቸው ጀምሮ እስከ ገራፊዎች ድረስ መንሰራፋቱን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል:: እንደውስጥ አዋቂ ምንጮቹ መረጃ ከሆነ የደህንነት ባለስልጣኖቹ የተዘፈቁበት የሙስና ተግባር በተጨማሪ ዘረፋን እና ሴት መድፈርን እንዲሁም የቡድን ወንጀሎችን ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል::በተለያዩ ከተሞች የሚገኙ ባለሃብቶችን በማስፈራራት ከፍርድ ቤት ትእዛዝ ውጪ በማሰር እንዲሁም የሙስና ወንጀል ተገኝቶብሃል ይህን ያህል ገንዘብ አምጣ ካላመጣህ እንገድልሃለን እስከማለት በከመድረሳቸውም በተጨማሪ ይህንን ጉዳይ ለፖሊስ የጠቆመ ባለሃብት በማፈን ንብረቱ ባማገድ እና በተለያዩ ስልቶች የተጠየቀውን ገንዘብ እንዲሰጥ በማስገደድ ላይ መሆናቸውን ምንጮቹ ጠቁመዋል::

ከዚህ ቀደም በሙስና የተከሰሱ የስርኣቱ ባለስልጣናትን ተገን በማደርግ በአዲስ አበባ ውስጥ የሚገኙ ባለሃብቶችን በመከታተል እና ደህንነት ቢሮ ድረስ በመውሰድ በሙስና ከታሰረው ስም እየተጠቀሰ ... ከሚባል ባለስልጣን ጋር ግንኙነት አለህ ማስረጃ ተገኝቶብሃል በማለት በፈጠራ ወንጀል ባለሃብቱን በመዝረፍ ስራ ላይ ተሰማርተው የነበረ እና እንዲሁም የአዲስ አበባን ቆነጃጅት ቢሯቸው ድረስ በግብረአበሮቻቸው አፋኝነት እና አስገዳጅነት በመውሰድ ካለፍላጎታቸው አስገድደው በመድፈር ላይ ናቸው ያሉት ምንጮቹ ተራ የደህንነት አባላት ለዚሁ ተልእኮ ተሰማርተው የሚሰሩት ምንም አይነት ወንጀል በቡድን ሲፈጽሙ የሚጠይቃቸው አለመኖሩን የሕዝቡን በደል የከፋ አድርጎታል::

ኢትዮጵያውያን በሕወሓቱ የደህንነት መዋቅር የሚመራ የሽብር ተግባራትን አጥብቆ ስለሚፈራ እና በየጊዜው በሕወሓት ደህንነቶች መሪነት የሚወሰዱ እርምጃዎች በሃገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ ስጋትን በመፍጠራቸው በየእስር ቤቱ የሚካሄዱ ሕገወጥ ጸረ ፍትህ ተግባራት እና የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የኢትዮጵያውያን የቀን ተቀን አጀንዳ ሆነው መምጣታቸው ገዢው ፓርቲ ሕዝቡን ምን ያህል እንዳሸበረ ይጠቁማል ሲሉ ምንጮሹ አክለው ገልጸዋል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሕወሓትን ሳይጨምር ብኣዴን ኦሕዴድ ደኢሕዴግ እና አጋል የክልል ጎሳ ፓርቲዎች ከአቶ ደብረጺሆን በሚወርድ ትእዛዝ ካልሆነ በስተቀር ምንም አይነት እርምጃ በፍቃዳቸው መፈጸም እንደማይችሉ ተነግሯቸዋል:: በቅርቡ የአቶ አለማየሁ አቶምሳን ሞት ተከትሎ አፈጻጸሙ በዶ/ር ደብረጺሆን መልካም ፍቃድ እንደሆነ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የተባለው የኦሕዴድ ሙክታር ከድር አቶ አለማየሁ ደክመው እያየ እና እያወቀ ሆስፒታል እንዲሄዱ አስቸኳይ ትብብር እንዲደረግ ወይዘሮ አስቴር ማሞ ስትጠይቀው ለዶ/ር ደብረጺሆን ነግረሽ አስፈቅጂ በማለት ሕወሓት በኦሕዴድ አናት ላይ ምን ያህል እየሸና እንዳለ እንዲሁም በሞራላቸው አመራሮቹ እንዳይራመዱ እያደረገ እንዳለ ፍንትው አድርጎ ያሳየ ነው:: ማንኛውም የኢሕኣዴግ አባል እና አጋር ድርጅት በድርጅቱ ሊቀመንበር ወይንም ምክትል አማካኝነት በቅድሚያ ለዶ/ር ደብረጺሆን ሪፖርት ማድረግ እና ሁኔታው ታይቶ ፈቃድ እና ውሳነ ካልተሰጠው በስተቀር መፈጸም እንደማይችል ትእዛ መተላለፉ ሲታወቅ በአዲስ አበባ እና በክልል ያለው የፍርድ ቤቶች እና የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ በአለቃ ጸጋይ በርኸ ስር ክትትል እየተደረገ እርምጃ የሚወሰድበት መሆኑ ሲታውቅ የጦር ሰራዊቱን በተመለከት በተዋረድ የሚያስተዳድሩ የወታደራዊ ደህንነት የሕወሓት መኮንኖች ተደራጅተው በየእዙ መመደባቸው ታውቋል::

ለሩጫ ውድድር የወጡ ሰቶች ያሰሙትን ተቃውሞ ተከትሎ ወደ እስር በት ተጋዙ

የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ እና የድርጅት ጉዳይ ሃላፊው ከሴቶቹ ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ 
ዛሬ በተካሄደው የሴቶች 5ሺሜትር ሩጫ ላይ የሰማያዊ ፓርቲ የሰቶች ጉዳይ ባመቻቸው እድል የፓርቲው ሴቶች የሮጡ ሲሆን በሩጫውም ላይ የተለያዩ መፈክሮች ማለትም እርዮት ትፈታ እና ሌሎች ማህበራዊና ፖለቲካዊ ጥያቄዎች አሰምተዋል::

ከመነሻው የጀመረው የተቋውሞ ድምጽ እስከ ማብቂያው የቀጠለ ሲሆን ሩጫቸውን ጨርሰው ሊገቡ ሲሉ በፖሊሶች ተቆርጠው በአሁኑ ሰዐት ታስረው ይገኛሉ በሩጫው ወቅት ተቋውሞ ሲያሰሙ የሚያሳይ ቪድዮ እና ፎቶ እንደደረሰን ምንለቅ መሆኑን በትህትና እንገልጻለን::



የሰማያዊ ፓርቲ የሴቶች ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሴት አባላት እና ከእናርሱ ጋር የነበሩ ሴቶች በዛሬው እለት በተካሄደው ሩጫ ላይ ተሳትፈው ሃሳባቸውን በመግለጽ ላይ አንዳሉ በሩጫው መጨረሻ ላይ በፖሊስ ታፍሰው ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአከባቢው የነበሩት የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ብርሃኑ እና የድርጅት ጉዳይ ሃላፊው አቶ ጌታነህ ሴቶቹ መታሰራቸው ምንም አግባብነት እና ህጋዊ መሰረት የለውም በማለታቸው ከሴቶቹ ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ አቤል ኤፍሬም በአከባቢው ስለነበሩ ብቻ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ያሉበትን ለማጣራት የሰማያዊ ወጣት ክንፍ አባላት በእንቅስቃሴ ላይ መሆናችንን እያስታወቅን የደረስንበትን ይፋ የምናደርግ መሆኑን እናስታውቃለን፡
ትግሉን በእስራት እና በግድያ ማስቆም አይቻልም!!