Search This Blog

Sunday, February 2, 2014

ኢትዮጵያዊያን አንድ ሆነን ለነፃነት መታገል ያስፈልጋል!!

ቃልኪዳን ካሳሁን (ከኖርዌ)
እንደሚታወቀው ኢትዮጵያዊያን በመላው አለም እንደሚኖሩ ይታውቃል። ከኦሮሚያ ይሁን ከአማራ፣ ከሶማሌ፣ ከደቡብ ፣ አፋር፣ ትግራይ፣ ቤኒሻንጉል፣ ድሬ . . . . . . .. ብቻ ከየትም ይምጡ የሁሉም ኢትዮጵያዊ የስደት መንሾ “በፖለቲካ አልያም የተሻለ ህይወት ፍለጋ” ከመሆን አይዘልም።
(በሀገሩ መኖር ማን ይጠላል . . . . . . . )Kalikidan
ብዙ ጊዜ የማስበው ታዲያ ኢትዮጵያውያኑ በሰው ሀገር ሲኖሩ እንዳውም ከሀገር ውስጥ የበለጠ አንድንትና መግባባት ወይም አብሮ የመኖር ስሜት ይኖራቸዋል። በሰው ሀገር የመኖርን የህይወት ትግል ለመላመድና ለማሸነፍም ከሀገር ልጅ የበለጠ አለኝታ፣ አይዞህ/ሽ ባይ እና አጋዥ የለምና። በተለያዩ አጋጣሚዎች የምንሰማው ግን ከዚህ በተቃራኒው የሆኑ እውነታዎችን ነው። በጥርጣሬ መተያየት፣ የብሄርና የፖለቲካ ክፍፍል………ሌላም ሌላም።
እርግጥ ነው ሁላችንም አንድ አይነት አቋም ሊኖረን አይችልም፡ ከመሰረታዊ ጉዳዮች በስተቀር በእያንዳንዱ ጉዳይ ላይ የግድ ተመሳሳይ ሀሳብ እንዲኖረንም አይጠበቅም። የተለያየ የፖለቲካ አቋም ሊኖረን ይችላል፣ የተለያዩ ብሄሮች ልጆችም ልንሆን እንችላለን፣ ኢትዮጵያውያን በመሆናችን ግን እነዚህ ሁሉ ነገሮች በህልውናችን ላይ አንዳች ጥላ ማጥላት የለባቸውም። ደግሞም ከተቀራረብን እነዚህ ሁሉ ነገሮች ሊታረቁና ሁላችንንም የሚያስማሙ ሀሳቦችን ለመፍጠር ይችላል። የአፍሪካ የነፃነት ምሳሌ የሆንን ዜጎች ህብረ ብሄራዊ ውበታችንን በእያንዳንዳችን ማንነታችን ላይ ካለው ኢትዮጵያዊነታችን ጋር የተጣበቁ የጋራ ተቀፅላዎችችን (stereotypes) በማጥፋት የትም ቦታ አንገታችንን ቀና አድረገን ለመኖር ምቹ ሁኔታዎችን ልንፈጥርበት ይገባል።
ልዩነቶቻችን በማቻቻል የትም ይሁን የት በአንድነት መስራቱ ለዜጎቿ ለኑሮ ምቹ የሆንች ኢትዮጵያን ለመፍጠር ዳግም ኢትዮጵያን ታላቅ ለማድረግ ያስችለናል። ይህም በቅርቡ እውን እንደሚሆን ተስፋ አለኝ። ይኸው ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያስተዳድረው ወያኔ/ህውሃት የህዝብ መብት በመንቀፍ፣ ዘረኝነትን በማስፋፋት፣ ሀገርን በመከፋፈል፣ ጎሰኝነትን በማስተማር፣ ሀገር በመዝረፍ፣ ሀገርን በመሸጥ፣ ሰውን ከሚኖርበት ቅዬ በማፈናቀል፣ በመቻቻል እንዳይኖር በማድረግ፣ ዘር ከዘር ጥላቻን ማስፈን ቀጥሎበት ሃያ ሁለት ዓምታትን አስቆጠረ። እስከመቼ ይኸን ነገር ዝም ብለን ማየት እንችላለን።
እዚህ ጋር የሌሎች ሀገራት ዜጎችን በሚያስቀና መልኩ አብሮ የመኖርና የመተባበር ባህልና ማህበራዊ ህይወት ያላቸው ባህር ማዶ አደር ኢትዮጵያውያን እንዳሉ መዘንጋት የለበትም። ይሁንና እነሱም ቢሆን እነዚህን መሰል በኢዮጵያውያን እህትና ወንድማማቾች መካከል እየተፈጠረ ያሉ ችግሮች ለመፍታት መንቀሳቀስ ይኖርባቸዋል።
ነፃነታችንን የቀሙን የወያኔ ዘረኞች ነፃነታችንን እንደቀሙን ለረዥም አመታት ለመግዛት እንዲመቻቸው በዘር፣ በቋንቋ፣ በክልልና በሃይማኖት ከፋፍለውን ከሃያ አንድ ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የጀመሩትን እስራት፣ ስደት፣ ግድያና ዝርፍያ አሁንም እንደቀጠሉ ነው። የወያኔ ዘረኞች ነፃነታችንን ቀምተው እየገዙን ቢሆንም ገዛናቸው ብለው እጃቸውን አጣጥፈው አልተቀመጡም። ዜጎች ነፃነታቸውንና መብታቸውን እንዳይጠይቁ አፋቸውን ያዘጋሉ፣ አንዱ ለሌላው እንዳይቆም ሀገር፣ ባንዲራና ኢትዮጵያዊነት የሚባሉ ትላልቆቹን የጋራ እሴቶቻችንን በየቀኑ ያፈረሳሉ።
ይህ የሚያሳየን ዜጎችን ትልቅ ተስፋ ይዘው ቤተሰብ መስርተው ለራሳቸውና ለሀገራቸው የሚኖሩበት ጊዜ እየጠፋ ተስፋ መቁረጥ፣ ስደትና የመከራ ኑሮ ዘመን እየከበበን መምጣቱ ነው።
ይህ ከሆን የነገዋን የነፃነት፣ የፍትህ፣ የዴሞክራሲ ባለጸጋ ኢትዮጵያን ለማየት እያንዳንዱ ዜጋ በቻለው አቅሙ ሁሉ ጠንክሮ በመታገል እና ከራሱ ባለፈ ሌላው ዜጋ የነፃነት ትግሉን ጎራ እንዲቀላቀል ብሎም የዚህ ትግል ባለቤት እንዲሆን ያስፈልጋል። የሀገራችን ህዝብ የነፃነት ችቦ አቀጣጣይ የትግሉ አካል በመሆን መስራት እንጂ ከቶ ሌላ አካል፣ ሌላ ሃይል መቶ ነፃ ያወጣኛል በሚል በባርነት እየተገዛ መጠበቅ የለበትም። ነፃነትና ዴሞክራሲ በችሮታ አሊያም ከሰማይ እንደሚወርድ መና የሚጠበቅ ስጦታ አይደለም። ነፃነት የራስን መስዋአትነት ይጠይቃል።
አለበዚያ “ላም አለኝ በሰማይ ወተትዋንም አላይ”እንዳይሆን ያስፈልጋል።
ነፃነት እኛ ሰዎች በልደት ወደዚህ አለም ስንመጣ አብሮን የሚመጣ የተፈጥሮ ፀጋ ነው። ነፃነት ከሌሎች የምንጠብቀው ወይም ማንንም ስጠን ብለን የማንጠይቀው ፈጣሪ ለእያንዳንዳችን ያደለን በዚህ አለም ቆይታችን ለደቂቃም ቢሆን እንዲለየን መፍቀድ የሌለብን ሀብት ነው። ነፃነታችን እጃችን ላይ ሲኖር በግለሰብ ደርጃ የምንደሰተበት፣ እንዳንቀማ በጋራ የምንጠብቀውና እንደወያኔ አይነቱ ፀረ ህዝብ ሃይል ሲቀማን ደግሞ በጋራ
ታግለን ማስመለስ የሚገባን የግልና የጋራ ሀብት ነው።
ዛሬ ከ22 የወያኔ አመታት በኃላ እኛ ኢትዮጵያውያን በድህነትና በረሃብ የምንጠቃው በዘረኝነት አለንጋ የምንገረፈው፣ የምንሰደደው፣ የምንታሰርውና የምንገደለው ይህንን ፈጣሪ ያደለን ነፃነት የሚባል ሀብት ወያኔ አንድ ሁለትና ሶስት እያለ ሲቀማን አፋችንን ዘግተንና እጃችንን አጥፈን ስለተመለከትን ነው። መፈናቀላችን፣ ስደታችን፣ ውርድታችንና በገዛ ሀገራችን ሁለትኛ ዜጋ ሆኖ መኖራችን እንዲያበቃ ለማድረግ ያለን ብቸኛ አማራጭ
ሌሎች መጥተው ነፃ ያወጡናል ከሚለው አመለካከት ተላቅቀን ነፃነታችንን ለማስመለስ ህዝባዊ ትግሉን መቀላቀል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ህዝብ በወያኔ የዘር በትር አለንጋ የሚደርስበት ግርፋት፣ ስቃይ፣ ረሃብ፣ ስደት፣ እንግልት በራሱ በህዝቡ ላይ ነው። ስለዚህ ህዝቡ ራሱ ለራሱ ነፃነት በእምቢ አልገዛም ባይነት የሚነሳበት ጊዜው አሁን ነው። ነፃነትን ከነፃ አውጭዎች በመጠበቅ እስከመቼ የወያኔ የጥይት ሰለባዎች እንሆናለን? ወገን ሁሉ ለራሱ ነፃነት፣ ህልውና ሲል የለውጡ እንቅስቃሴ ታጋይ የመሆን ኢትዮጵያዊ ግዴታውን እንዲፈጽም ጥሪ ማድረግ ይገባል። ለሀገሩ፣ ለማንነቱ መሰዋትነት ለመሆን እንደሚኮራ ሁሉ ሀገሩም በሱ ትኮራለች። ወያኔ በ22 ዓመት ውስጥ የሰራው ወንጅል በወገናችን ላይ እንዲህ በቃላት ተዘርዘሮ አያልቅም። ይህ አልበቃ ብሎን።
ታዲያ ምንድ ነው አንድ ሆንን ከመታገል ፈንታ መለያየትን መረጥን!

No comments:

Post a Comment