Search This Blog

Monday, February 10, 2014

እነ አቶ ጌቱ ገለቴ ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ተወሰነ


በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል ተፈልገው በጋዜጣ ጥሪ የተደረገላቸው የ“ጌታስ ኢንተርናሽናል” ከፍተኛ ባለአክሲዮን አቶ ጌቱ ገለቴን ጨምሮ ሌሎች ያልተያዙ ተጠርጣሪዎች፣ በጥሪው መሰረት ባለመቅረባቸው ፍ/ቤቱ ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ሰሞኑን ብይን የሰጠ ሲሆን ችሎቱ የእነ አቶ መላኩ ፈንታን ጉዳይም ተመልክቷል፡፡ 
ከትናንት በስቲያ የዋለው ችሎት፤ ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ትዕዛዝ ያስተላለፈባቸው አቶ ጌቱ ገለቴን ጨምሮ የገቢዎችና ጉምሩክ ሰራተኞች  አቶ ታደሠ ፈይሣ፣ ገዳ በሽር እና ነጋ ቴኒ የቀረበባቸው ክስ፤ ከቀረጥና ታክስ መቀነስና ማስቀነስ ጋር የተያያዘ መሆኑ ይታወሳል፡፡ 
በእለቱ በቀጠሮአቸው መሠረት ችሎት፣ የቀረቡት፤ የቀድሞ የገቢዎችና ጉምሩክ ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ እና ምክትላቸው አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ጨምሮ በመዝገቡ የተካተቱ ከፍተኛ ኃላፊዎች እና ባለሃብቶች፤ የክስ መቃወሚያቸውን ያቀርባሉ ተብሎ የተጠበቀ ቢሆንም አንዳንዶቹ አልደረሰልንም በማለታቸውና ተጨማሪ 10 ቀን በመጠየቃቸው፣ ፍ/ቤቱ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ የሁሉንም ተከሳሾች መቃወሚያ ለመስማት ለየካቲት 10 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡ 
በሌላ በኩል የቀድሞ የደህንነት ኃላፊ በነበሩት በአቶ ወ/ሥላሴ መዝገብ፣ ህገወጥ ሃብት ይዞ መገኘት በሚል የተከሰሱ ተከሳሾች ላይ አቃቤ ህግ ክሴን ላሻሽል በማለቱ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ ለየካቲት 3 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡

No comments:

Post a Comment