Search This Blog

Saturday, February 22, 2014

የኢትዮጵያ አየር መንገድ መጠለፍ እና ወያኔ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራ መጠለፉን ተከትሎ የአየር መንገዱ ተጠቃሚዎች ቁጥር ይቀንሳል ተብሎ ይገመታል። ይህን የተረዱት የወያኔ ሹማምንት መክረው ዘክረው የደረሱበት ስልት ቢኖር የረዳት አብራሪውን ቤተሰቦች በማስፈራራትና በማግባባት ረዳት አብራሪው አእምሮው የታወከ “እብድ” እንደሆነ እንዲናገሩ ማድረግ ነው።
የረዳት አብራሪው እህት “ወንድምሽ ጭቅላቱን ያመው ነበር ብለሽ ከተናገርሽ በንጻ ይለቀቃል” የሚል ምክር በተላኩ የደህንነት ሰዎች እንዲደርሳት የተደረግ ሲሆን ሌሎችም የቤተሰቡ አባላት እሷ የተናገረችውን እንዲደግፉ ወያኔ ጫና እያደረገባቸው ነው።
በዚሁ መሰረት ጫና ተደርጎባችው ይሁን የብአዴን አባል በምሆናቸው ምክንያት ዶ/ር እንዳላማው የተባሉ የረዳት አብራሪው ወንድም ቪኦኤ ላይ ቀርበው ምንም እንኳን ወንድማቸው የአእምሮ ሁከትም ሆነ ጭንቀት እንዳለበት እሳቸው ባያውቁም እህቱ ያለችውን ግን ሙሉ ለሙሉ እውነት ነው ብለው ደግፈዋል። (ወይንም እንዲደግፉ ተደርገዋል)።
እንደተለመደው በቪኦኤ በኩል “ረዳት ፓይለቱ አእምሮው የታወከ፣ እብድ ነው” የሚለውን ዜና የሰራው ጋዜጠኛ ሄኖክ ሰማእግዜር መሆኑ የዘገባው መልዕት በወያኔዎች እንደተጠነሰሰ ይበልጥ የሚያረጋግጥ ነው።
ይህ በዚህ እንዳለ በጀርመን ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ረዳት አብራሪ ሀይለመድህን እንደ ወንጀለኛ እንዳይታይና ጥገኝነትም እንዲሰጠው በሚል የድጋፍ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያደርጉ መዘጋጀታቸውን አሳውቀዋል።
Ethiopian Airlines flight hijacked by it's pilot

No comments:

Post a Comment