Search This Blog

Monday, February 10, 2014

አቶ አስራት ወደ ቅሊንጦ ወህኒ ቤት ተወሰዱ

አቶ አስራት ጣሴ በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ ለ3 ቀናት እንዲቆዩ ከተደረገ በኋላ ምክን ያቱ ለጊዜው ግልፅ ባልሆነ ውሳኔ ወደ ቂሊንጦ ከፍተኛ ጥበቃ ወህኒቤት እንዲዛወሩ መደረጉን የፍኖተ ነፃነት የፖሊስ ምንጮች አሳውቀዋል፡፡

የፖሊስ ምንጮቹ እንዳሉት ኦአስራት በፖሊስ ጣቢያው በቆዩባቸው ጊዜያት በእስረኛው ተገቢው አክብሮትና መልካም አቀባበል ማግኘታቸው አሳሪዎቻቸውን አላስደሰተም፡፡

አንድነት ፓርቲን ከምስረታው ጀምሮ በከፍተኛ አመራርነት ሲያገለግሉ የቆዩትና በአሁኑ ወቅትም በፓርቲው ብሔራዊ ምክር ቤትና ስራ አስፈፃሚ የፓርቲዎችን ውህደት እንዲመሩና የአማካሪ ምክርቤት እንዲያቋቁሙ ኃላፊነት የተሰጣቸው መሆኑ ይታወቃል፡፡ አንድነት “የሚሊዮኖች ድምፅ ለፍትህ” በሚል መሪቃል የመንግስት የተለያጡ ሀላፊዎችን ለመክሰስ እንቅስቃሴ ማድረጉን ተከትሎ መንግስትም የአንድነት ፓርቲ አመራሮችን ምክንያት እየፈለገ መክሰስና ማሰር መጀመሩ ገዢው ፓርቲ አለመረጋጋት ውስጥ እንደገባ የሚያመላክት ነው፡፡

No comments:

Post a Comment